December 10, 2018
2 mins read

ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ወጣቶች ላይ የቀረበውን የሽብር ክስ ውድቅ አደረገው

የኦነግን አቀባበል ምክንያት በማድረግ በቡራዩና አካባቢው ተከስቶ በነበረው ግጭት የተጠረጠሩ የአዲስ አበባ ወጣቶች ላይ የቀረበውን የሽብር ክስ ፍርድ ቤቱ ውድቅ አደረገው፡፡

በመሆኑም በተጠርጣሪዎቹ ላይ የግድያ ወንጀል ክስ ሊመሰረት ነው። በከፍተኛው ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎች በዛሬው እለት 17 ያህል ተጠርጣሪዎች የቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤቱም የቀረበባቸው ክስ የሽብር ወንጀልን አያሟላም በማለት በግድያ ወንጀል ክስ እንዲመሰረትባቸው ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ ጉዳያቸውም ከዚህ በኋላ በሶስተኛና ሃያኛ ችሎት እንዲታይ ወስኗል፡፡ ይህ ውሳኔ መሰጠቱ በተጠርጣሪ ቤተሰቦች ዘንድ በተወሰነ ደረጃ ደስታን የፈጠረ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ምክንያቱም በሽብር የተጠረጠረ ምንም ዋስትና የማይፈቀድለት ከመሆኑም በላይ ጉዳዩ የተንዛዛና ረጅም አመት የሚፈጅ፣ እንዲሁም በጅምላ የሚፈርጅ ይሆን ነበር፡፡ ወደግድያ ወንጀል መቀየሩ ግን የእያንዳንዳቸውን ጥፋት በተናጠል በማስረጃ እንዲጠየቁ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ ካለጥፋታቸው የታሰሩም የሚፈቱበትን እድል ያመቻቻል ሲሉ አንድ የህግ ባለሙያ ለዘሃበሻ ተናግረዋል፡፡ ዘሃበሻ የአዲስ አበባ ወጣቶች ክስ ሽብርተኝነት መሆኑን በብቸኝነት ሲዘግብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ዛሬ ክሱ ወደግድያ ከተቀየረ በኋላ ግን በርካታ የመንግስት ሚዲያዎች ክሱ ሽብርተኝነት እንደነበር ዛሬ እንደአዲስ እየዘገቡት ነው፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=mCS4y1SnXxw

Previous Story

«የቅማንቶች ጥያቄ» ነበር. . . | አቻምየለህ ታምሩ

93123
Next Story

ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባ ሊደረጉ የነበሩት ህዝባዊ ሰልፎች ተራዘሙ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop