September 30, 2022
3 mins read

ወደ አዲስ አበባ የመግባት መብታችን ይከበር!    ሁለተኛ ቀን ደጅ ጥናት

teregnaw Oromoትናንትና እንዳጫወትኳችሁ አዲስ አበባ አትገቡም ተብለን ወደ ደብረ ብርሃን ከተመለስን በኋላ የዞኑ አስተዳደር ቢሮ መላ ይፈልግልን ስንል ደጅ ጥናት አምሽተን ምንም መፍትሄ ሳናገኝ ተበታትነን አደርን።
ዛሬ ጠዋት ማለዳ ላይ ቁጥሩ አያሌ የሆነ ህዝብ የሰሜን ሸዋ ዞን ፅህፈት ቤት ደጃፍ ላይ ተሰብስቦ እንደገና ደጅ ሲጠና ነበር። ይሁን እንጂ ያነጋገርናቸው ባለስልጣናት ነገሮች ከአቅማቸው በላይ እንደሆነ ገልፀዋል። ይሁን እንጂ ህዝቡ በእንባና በቁጣ ቁጭቱን ገልጿል። ዛሬስ እንዴት አማራ የሚቆረቆርለትና መከታ የሚሆነው መሪ አጣ የሚለው ድምፅ ከፍ ብሎ ሲሰማ ነበር።
ብዙዎቹ የአዱስ አበባን መታወቂያ ለባለስልጣናት እያሳዩ የደረሰባቸውን በደል ቢገልፁም ያገኙት አንዳች መፍትሄ የለም። ሌላው ቀርቶ ከነዚህ ተጓዦች መሃል ምንም ቤሳቤስቲ የሌላቸውን ማረፊያ ፈልጉላቸው የሚሉ ድምፆች ቢሰሙም ዘወር ብሎ የሚያይ መሪ ጠፋ።
ይሁን እንጂ አንዳንድ እመጫቶችና ልጃገረዶች የሚያርፉበትን ቦታ ስናፈላልግ የቁልቢ ፔንስዮን ባለቤት አልጋና ተፈላጊ ነገሮችን ለማሟላት ቃል ገብተው እነሆ የተወሰኑ ወገኖች በዚያ አርፈዋል። በዚህ አጋጣሚ ከዚህ ፔንስዮን ባለቤት ጋር ያስተዋወቀኝና እህቶቻችን ማረፊያ እንዲያገኙ ምክንያት ለሆነው ወንድም ምስጋናዮ ከፍ ያለ ነው።
 ሌሎቹን ብዙ ወገኖች እንግዳ ተቀባይ የሆነው የደብረ ብርሃን ህዝብ በአንድም በሌላም መንገድ ረድቶልናልና እግዚአብሔር ይባርክልን።
አሁንም መቼ ወደ አዲስ አበባ መግባት እንደምንችል አናውቅም። እዚሁ ሆነን ሁኔታውን እየተከታተልን ነው። ዛሬ በነበረን ስብሰባ ላይ ብዙዎች መራራ እንባ ሲያነቡ ማየት ምንኛ ልብ ይሰብራል። አማራ በእውነት ለመብቱ የሚታገሉ መሪዎችን ያላገኘ ህዝብ ነው። ያሳዝናል።
ገለታው ዘለቀ
ደብረብርሃን

Leave a Reply

Your email address will not be published.

4U54U54I59I4590
Previous Story

ዒላማውን የሳተ የፖለቲካ ትግል ድግግሞሽ እና ውጤቱ – ጠገናው ጎሹ

የአቢይ አህመድ ጨለማ ጉዞ!
Next Story

የኦነግ/ኦህዲዶች አይኪው ቢለካ … ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop