July 27, 2022
2 mins read

በአንድ ራስ ሁለት ምላስ – እኝህ አቢይ አህመድ የፖለቲካ ሞተራቸው ነክሶባቸው ይሆን እንዴ?

የተከበሩ አቢይ አህመድ ሁለት የተለያዩ አስተሳሰቦችን ባንድ ጊዜ፤ ሁለት አይነት እንቅስቃሴና ለሁለት የተከፈለ ባህርይ የሚያጣምር የአይምሮ ችግር ወይም የመገለልና የማንነት ቀውስ (dissociative identity disorder (DID)) ይኑራቸው አይኑራቸው በእርግጠኝነት መናገር አልችልም:: ነገር ግን ካስተዋልኳቸው ነገሮች በእርግጠኝነት በአንድ ራስ ሁለት ምላስ (Doublethink) ወይም ድርብ ተፃራሪ አስተሳሰብ ባለቤት መሆናቸውን እረዳለሁ::
ታላቁ ጆርጅ ኦርዌል 1984 በተሰኘው መፅሃፉ “በአንድ ራስ ሁለት ምላስ (Doublethink) ወይም መንታ ተፃራሪ አስተሳሰብን ሲገልፀው ‘ሁለት ተቃራኒ የሆኑ ሀሳቦችን በአንድ ጊዜ መያዝና ሁለቱም ተፃራሪ ሀሳቦች እውነት ናቸው ነው ብሎ ማመንና አመራርንና ህዝብ ስነልቦናዊ መጠቀሚያ በማድረግ የሚከወን የፕሮፖጋንዳ አካል ነው” ይላል:: በመቀጠልም “በአንድ ራስ ሁለት ምላስ (Doublethink) አስተሳሰብ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ እንደ ፓርቲ ህዝቡ የራሱን ግንዛቤ እንዳይጨብጥ ህሊናውን የሚቆጣጠርበት ዘይቤ ወይም ብልሃት ነው:: በተጨማሪም ህዝቡን ለማሳመን ህዝቡ እውነትነቱን ከሚያውቀውን ጉዳይ ተቃራኒውን በማስቀመጥ እውነትን መበረዝና ማዛባትም ነው:: በአንድ ራስ ሁለት ምላስ (Doublethink) ማወቅና አለማወቅን በጥንቃቄ የተቀመሩ ውሸቶችን በመደርደር አስፈላጊ የሆኑ መዘንጋቶች እንዲሰፍኑ ማድርግ እንዲሁም አስፈላጊ ሆነው ሲገኙ እንደገና ለትውስታ ማብቃት እንደገናም ማስረሳት ነው::” ሲል የዘረዘረው የድርብ አስተሳሰብ ይዘትን ያሰፈረበት ዝነኛ መጣጥፉ አሳምሮ በሚገባ ይገልፃቸዋል::
ይሄው ነው!

Hailu AT

1 Comment

  1. ኦርዌላዊ

    ከአብዮቱ በፊት (እኛ ሳንወለድ) በእንግሊዝ የኖረ

    ኦርዌል የተባለ ደራሲ ነበረ

    ገና ስለሚመጣው የጭቆና ዓለም

    በትንቢታዊ መልክ ያልጻፈው ጉድ የለም

    ሰውን ከብት አድርጎ በእሺታ ለመግዛት

    የኅሊናን ሚዛን ምኅዋሩን ማዛባት

    ገልብጦ ማሳመን ታቹን ብሎ ላይ

    ምድርንም ሰማይ

    ይሆናል አላማው

    የመጭው ቀን ገዢ ሲቀመጥ በማማው

    ብሎ ነበር ኦርዌል

    ዋዛ በሚመስለው የዚያኔ ድርሰቱ

    እንዲህ ሊያስደምመን

    ዛሬ በኛ ጊዜ ኦርዌላዊ ዐለም ፈጥኖ መከሰቱ

    እናማ

    ቀን ቀንን አራውጦ

    ባሕሩን ተሻግሮ አህጉርም አቋርጦ

    የኦርዌልም ትንቢት በኛ ደረሰና

    ጦርነት ሰላም ነው ውድመት ብልጽግና

    (እስር ነጻነት ነው ቅሌት ሥልጣኔ

    መፍረስ መገንባት ነው ብክነትም ምጣኔ

    ማነስ መደመር ነው

    አርበኛ ሲሳደድ ባንዳ ሆኖ አለኝታ

    ሌሊት ንጋት ተብሏል ውርደትም ከፍታ።

    አሁንገና ዓለማየሁ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

295282071 583582390082948 697601470007862189 n
Previous Story

ከሀገር ውጭ ለሚገኙ መቅደሶቻችን ታቦታትና ንዋያተ ቅድሳት ይዞ ለመሔድ ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን የመጀመሪያውም ብቸኛውም አባት አይደሉም

ap20072558121518 edit wide 8bba9eaf6080070e1716cbe1ea67a5c7d4609713 s700 c85
Next Story

ዕዉቀት አልባ  ወረቀት – የድንቁርና ጎርፍ !

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop