ጣዕራችን ይልቀቀነ – ፈ.ፉ

ምናልባት ዘመኑ ነው፣
አሊያም ዕድሜያችን ነው፣
ወይ ደግሞ እኛው ነን፣
በጊዜ አልባስ ተሸፍነን፣
ዛሬስ ደከመን፣ ሰለቸነ፣
በደመና በጭጋግ ተሽፈንነ፣
በማያልቅ የተስፋ ብርሃን፣
በሚለዋወጥ ውጋጋን፣
ተሞኘን፣ በቋንቋ ተታለልነ፣
በግምት ባህር ሰጠምነ !!!
************
ፈ.ፉ. (11 Jan 2022)
ተጨማሪ ያንብቡ:  በደም የጨቀዬው የሳሪዮስ መስቀል

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share