August 9, 2020
5 mins read

የአርባ ቀን መታሰቢያ ለአርሲና ባሌ ሰማእታት

ሁለት ቦታ ቀብርህ
ቀብርህ ሁለት ቦታ
የት ይቁም ሐውልትህ
ተዝካርህ የት ይሁን
አመድ ሆኗል ቤትህ
ዝክሩን ማን ይደግስ
ታርደው ልጅ እናትህ
ቀብርህ ሁለት ቦታ
ደም ሥጋ አጥንትህ
ከፊሉ ጅብ ሆድ ውስጥ ከፊሉ ጉድጓድ ውስጥ
የት ይቁም ሃውልትህ?
በምድር አልተመቸም
በኢዮር ይደረግ አርባና ፍታትህ።

አርባህን ማን ያውጣ?
ሞትህ በገጀራ
ፍታትሕ ባሞራ
ቀብርህ በጅብ ጎሬ
ርስትህን ሊቀሙ
ማተብክን እያዩ
ያረዱህ ገበሬ።
አርባህ ነገ ማልዳ
ማን ያወጣልሃል
ሚስትህ ልጅህ ታርዳ?
ወገን ያልከው ነስቶህ
በገዛ ሃገርህ መቀበሪያ ጉድጓድ
ከውቅያኖስ ማዶ
ሐዘን እንድረስህ
እንባችን ውቅያኖስ ለቅሷችን ነጎድጓድ
አንተም ቋሚው ምዉት
ተንቀሳቃሽ በድን
እኩልህ ተገድሏል እኩልህም ቢድን
ሰማንያህ ተቀዳ ቆንጨራው ሲቃጣ
አርባዋን አወጣህ አርባህን ማን ያውጣ
የቁርባኗ ሚስትህ እሷ ሳትከዳ
ተለይታህ ስትሄድ በገጀራ ታርዳ
የሞቷ ሰቆቃ የእርዷ ሰቀቀን
ባርባ ዓመት አይጠፋም ይቅርና ባርባ ቀን
አይዞህ እንዳንልህ እኛም እንዲህ ርቀን
ከሩቅ ሥጋ ዘመድ ጎረቤት ይበልጣል ይሉን ነበር አበው
ጎረቤት ናቸው ወይ የሚያስጨፈጭፉህ ቤተሰብህን ከበው።
ንብረትም ይዘረፍ ሕንጻንም ያቃጥሉ ምን አገኙ ገድለው
የትኛው ጣዖት ነው የዚህ ሁሉ ክርስትያን ደም ይምጣልኝ ያለው?

ለገዳይ እንጸልይ
ባንቺ አልተጀመረም የመስቀል መከራ አርሲ ሻሸመኔ
ክርስትያን ሲሳደድ ሲሰየፍ ሲታረድ ኗሯል በአረመኔ
ጻድቁን የዋሁን ቸሩን ምስኪኑን ሰው ሲነግረን ስንክሳር
ቆርጠው ፈልጠውታል በጨካኞች ደቦ አይቷል ብዙ አሳር።
የክ/ርስትያን ቅዱስ ይሄ ነው ታሪኩ ተገልጦ ሲነበብ
በምድራዊ ሕይወት ስለ እምነት ጎስቁሎ በሰማይ ቤት ማበብ።
ስለዚህ አማኞች እውነትና ጽድቅን እንያዝ አጥብቀን
ፍትህ የሌለውን የምድራዊ መንግሥት ከንቱ ተስፋ ንቀን
በይቅርታ እንጽና ያምላካችንን ፍርድ በላጩን ጠብቀን።
ወገናችን ታርዶ
እስካንገት ብንሰጥምም በደሙ ማእበል
ይቅር ባይሉንም እኛ ይቅር እንበል
ክርስትና ማለት ይኸው ነው እውነቱ
በቀል አንፈልግም አያዝም እምነቱ
ይልቅስ ለገዳይ እንጸልይ እኛ
ጌታ እንዲያላቅቀው
ከኅሊና ደዌ ከዲያብሎስ ቁራኛ።

አንተም አይቀርልህ
የወንድም ርስት አምሮህ ገጀራ አንስተህ ደሙን አፍሰሃል
ባንተው ብሶ ደግሞ እስካለም ዳርቻ በለቅሶ ጮኸኻል።
ገለህ ስታለቅስ ፈረንጁን ቻይናውን ያሞኘህ መስሎሃል
በዚያው በገጀራህ ያንተም ጉድጓድ ማልዶ ተቆፍሮልሃል።
እንኳንስ ልትጨምር ያንተም ርስት ይሰጣል ለሌላ ተላልፎ
ምን ሲሻ መሰለህ በሀገርህ ዳርቻ ያለው አሰፍስፎ?
ይልቅ ከወንድምህ ተቀመጥ በሰላም
ሊነቅሉህ ቀርበዋል ክርስትያን ሆንክ እስላም::
ይሻላል ማስተዋል
ክርስትያን ሆንክ እስላም ሊነቅሉህ ቀርበዋል
ሀገርህን በሞላ ዙሪያዋን ከበዋል።
ዛሬ በገጀራ ብትጨፈጭፍ ወንድም
ከባሕሩ ዳርቻ እያዩህ ነው አግድም
አንተም በበሽታ በጦር ስትወድም
በሰሰትክለት ርስት ቆሞ አይቀርም አንድም።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

109307
Previous Story

«አዲስ አበባን አላስፈላጊ እናደርጋታለን፣ ኢትዮጵያን እንድትመቸን አድርገን እንሠራታለን፣ ብልጽግና እንዲጠቅመን አድርገን መሥርተነዋል» (ሺመልስ አብዲሳ)

109337
Next Story

ከሚገድለኝ ሰይጣን ይልቅ የሚሰድበኝ ባለስልጣን ይሻለኛል! – ስዩም ተሾመ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop