February 23, 2019
2 mins read

በአሜሪካ አሌክሳንድሪያ ቨርጂኒያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑት አቶ መርጊያ ንጉሴ ፍርድ ቤት ቀርበው ጥፋተኛ ተባሉ

94224

በአሜሪካ አሌክሳንድሪያ ቨርጂኒያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑት አቶ መርጊያ ንጉሴ ትንናት ፍርድ ቤት ቀርበው ጥፋተኛ ተባሉ፡፡

https://youtu.be/9_PNwyW18Qg

የ58 አመቱ አቶ መርጊያ ጥፋተኛ የተባሉት በማጭበርበር የአሜሪካ ዜግነት አግኝተዋል በሚል ነው፡፡ በዛሬው እለት የተሰየመው ፍርድ ቤቱ እንደገለፀው አቶ መርጊያ በቀይ ሽብር ወቅት ተጠርጣሪ እስረኞችን ደብድበዋል፣ ገርፈዋል፣ አሰቃይተዋል፡፡ ይህ ድርጊት የተፈፀመባቸው ግለሰቦችም ለዘላቂ ጉዳት ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡

 

ይሁንና በ1999 እ.ኤ.አ ወደ አሜሪካ በገቡበት ወቅት ለኢምግሬሽን ሰራተኞች ሙሉ በሙሉ ውሸት የሆነ ታሪክ ተናግረው የስደተኝነት ፈቃድ ማግኘታቸውንና በ2008 ደግሞ የአሜሪካ ዜግነት እንደተሰጣቸው ፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡ የአሜሪካ ዜግነት ለማግኘት ቃለመጠይቅ በተደረገላቸው ወቅት ማንንም ሰው በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት እንዳላሰቃዩ ተናገረው የነበረ ቢሆንም ለፍርድ ቤቱ ግን ያንን ያሉት በሀሰት እንደነበር አምነዋል፡፡ በአሜሪካ ህግ መሰረት በሀሰት መግለጫ ዜግነት ማግኘት ክልክል በመሆኑም የጥፋተኝነት ውሳኔ እንደተላለፈባው ፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ የአሜሪካ ረዳት ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቤንዝኮወውስኪ እንደተናገሩት ከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅመው ራሳቸውን ደብቀው አሜሪካ ለሚኖሩ ሰዎች ምንም ምህረት የሌለ ሲሆን ሌሎች እንደ መርጊያ አይነቶችም ታድነው ለፍርድ ይቀርባሉ፡፡ አቶ መርጊያ የፊታችን ሜይ 17 ቀን ፍርድ እንደሚሰጣቸው ለመረዳት ችለናል፡፡

94221
Previous Story

አዴፓ በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ላይ ጠንካራ አቋም እንዳለው አስታወቀ

94227
Next Story

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተቃዋሚዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop