February 21, 2019
2 mins read

አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ለፍርድ ቤት ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት አገኘ

94201

በቅርቡ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉትና ክስ የተመሰረተባቸው አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ይሟሉልኝ በማለት ለፍርድ ቤቱ ያመለከቷቸው አቤቱታዎች ነበሩ።

https://www.youtube.com/watch?v=9K1EwuewSOA

ከነዚህ መካከል በቁጥጥር ስር ከመዋላቸው በፊት የጀመሯቸውን ስራዎች ከማረሚያ ቤቱ እየወጡ ለማከናወን የተወሰነ ጊዜ እንዲፈቀድላቸው፣ መጽሐፍትና መጽሔቶች ማረሚያ ቤት እንዲገቡላቸው መጠየቃቸው ይገኝበታል፡፡ ተከሳሹ የግል ኩባንያ የቦርድ ሰብሳቢና ስራ አስኪያጅ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ትልልቅ አገራዊ ጉዳዮችን ለማከናወን ውጥን ስራዎች ጀምረው እስከተያዙበት ዕለት ስራ ላይ እንደነበሩ አስረድተዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምደብ 15ኛ ወንጀል ችሎት በዛሬ ውሎው ተከሳሹ ያቀረቡትን አቤቱታ አድምጦ ትዕዛዝ ሰጥቷል። በዚህ መሰረት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ እንደማንኛውም የሙስና ወንጀል ተጠርጣሪ ማረሚያ ቤት መቆየት እንዳለባቸው ገልፆ ነገር ግን በአቤቱታቸው መሰረት ውጥን ስራዎቻቸውን ለመፈጸም የሚፈልጓቸውን ሰዎች ዝርዝር አሳውቀው ለአንድ ወር እንዲያገኟቸው ፈቅዷል።

94198
Previous Story

የጉራጌ ህዝባዊ ንቅናቄ(ጉህን) በዛሬው እለት መግለጫ አውጥቷል

94204
Next Story

‹‹ትላንት በመቀሌ አደባባዮች ሲሰድቡኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ወድጄዋለሁ፡፡ ዲሞክራሲ ነው፡፡›› ዶ/ር አብይ አህመድ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop