January 16, 2019
2 mins read

ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ላይ የዋይ ፋይ አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው

93760

ኢትዮ ቴሌኮም በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች ላይ የዋይ ፋይ አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡
https://youtu.be/epx_GOJUaUQ
በሁለቱ ኩባንያዎች መሀከል ስምምነቱ የተፈፀመ ሲሆን የዋይፋይ አገልግሎቱ ሲጀምር በአለም አቀፍና በአገር ውስጥ በረራዎች የሚሰጥ ይሆናል፡፡ የኢትዮ ቴሌኮም አለም አቀፍ ንግድ ኦፊሰሩ አቶ ሰይድ አራጋው ለካፒታል ጋዜጣ ሲናገሩ ‹‹ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ስምምነት ከፈፀምን በኋላ ለአገልግሎቱ ሳተላይት የሚያቀርብልን አለም አቀፍ ኩባንያ እያነጋገርን ነው›› ብለዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለም ኢትዮ ቴሌኮም እንደአዲስ ባቋቋመው በዚሁ አለም አቀፍ ንግድ ዲፓርትመንት አማካኝነት ከታዋቂ አፕሊኬሽኖች ጋር እየተደራደረ መሆኑን ኦፊሰሩ አስረድተዋል፡፡ ከእነዚህ አፕሊኬሽኖች መሀከል ፌስቡክና ዋትስ አፕ እንደሚገኙበት አቶ ሰኢድ ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ኢትዮ ቴሌኮም ከ27 አለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር የድምፅ አገልግሎትን በተመለከተ ስምምነት የፈፀመ መሆኑን የተናገሩት ኦፊሰሩ በቅርቡ ደግሞ በፊት በነፃ የነበሩት የፌስ ቡክና የዋትስ አፕ የፅሁፍ መልእክቶች ላይ አፕሊኬሽኖቹ እንዲያስከፍሉ ለማድረግ በድርድር ላይ መሆናቸውን ለካፒታል ጋዜጣ አስረድተዋል፡፡

93757
Previous Story

‹‹አሁን የህወሃት ሰራዊት አኩርፏል፡፡ ስራ በማበላሸት ላይ ናቸው፡፡” ኮ/ል ጌታቸው ብርሌ

93779
Next Story

የአሜሪካ እርዳታ በግማሽ ሊቀንስ ነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop