January 16, 2019
2 mins read

የኦነግ ጦር የደቡብ ዞን አዛዥ የሰላም ጥሪውን ተቀበለ

93739

በኦነግ ጦር የደቡብ ዞን አዛዥ የሆነው ኤሊያስ ጋምቤላ ጎሎ የቀረበለትን የሰላም ጥሪ ተቀበለ፡፡ በትላንትናው እለትም ወደሰላማዊ ትግል ተመልሶ ወደተዘጋጀለት ማረፊያ ገብቷል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=epx_GOJUaUQ

የሰላም ጥሪውን ያቀረቡት የጉጂ አባ ገዳዎች ሲሆኑ ጥሪውን ተቀብለው ሌሎች የኦነግ ሸኔ አመራሮች እየተመለሱ መሆኑም ታውቋል፡፡ የጉጂ አባ ገዳ ጂሎ መንኦ ዛሬ ለጋዜጠኞች ሲናገሩ ‹‹በጉጂ እና ምእራብ ጉጂ ዞን በተለያዩ ደረጃዎች ላይ የሚገኙ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ጦር አመራሮች የቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ወደተዘጋጀላቸው ማረፊያዎች በመግባት ላይ ይገኛሉ።› ብለዋል፡፡ አባ ገዳዎች ከመንግስት ጋር በነበራቸው ውይይት በተስማሙት መሰረት የዞኑ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ጦር ወደተዘጋጀላቸው አራት ካምፖች እየገቡ መሆኑን የጠቆሙት ጂሎ መንአ በመንግስት በኩል ያለውን ቀሪ ጉዳይም የአባ ገዳዎች ከመንግስት ጋር በመመካከር እንደሚጨርሱ አስረድተዋል፡፡ የጉጂ አባ ገዳዎች ባሳለፍነው ሳምንት አውጀውት የነበረው የሰላም ሳምንት በዚህኛው ሳምንትም እንዲቀጥል የተወሰነ ሲሆን ከሰላማዊ ትግል ውጪ የሚደረግ ማንኛውንም የትጥቅ ትግል ተቀባይነት እንደሌለው አባ ገዳዎቹ ገልፀዋል፡፡

93736
Previous Story

የክፍለ ከተማው ባለስልጣን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የህዝብ ገንዘብ ይዘው ተሰወሩ

93742
Next Story

አዲስ አበባ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተጠለሉ ተፈናቃዮች ግቢውን እንዲለቁ ተጠየቁ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop