November 27, 2018
2 mins read

የጋምቤላው ፕሬዚደንት ‹‹ከዶክተር አብይ ጋር ተደምረናል፡፡›› አሉ!

92776

አዲሱ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድርና የጋሕአዴን ሊቀመንበር ኡሞድ ኡጁሉ ከመንግታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ‹‹ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጋር ተደምረናል፡፡›› ሲሉ ተናገሩ፡፡ ጨምረውም ‹‹ለዚህ ማሳያው ባለፈው ሰፊ ጊዜ ተወስዶ በግምገማ አማካይነት የተደረገው ለውጥ በራሱ እማኝ ነው፡፡ ይህም ብቻ አይደለም በክልሉም የተለያዩ ድጋፎች እየተሰጡ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡

በጋምቤላ ክልል አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ቁልፍ ችግሮች መለየታቸውን የተናገሩት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በአዲስ አበባ ለ14 ቀናት በተካሄደ ግምገማ የፀጥታ ችግርና የልማት ፕሮጀክቶች መጓተት በክልሉ መስተዋላቸውን ገልፀዋል፡፡ ‹‹በክልሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችና ሙስና መንሰራፋት የክልሉን ህዝቦችና ወጣቶች ተጠቃሚነት ጎድቶታል፡፡›› ያሉት ርእሰ መስተዳድሩ በክልሉ አልሚ ካልሆኑ ባለሀብቶች መሬት እየተነጠቀ ወደ መንግሥት የሚመለስበት ሥራ እየተሠራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በዚህ መሰረት ንብረትነቱ የሼህ መሀመድ አል አሙዲ የሆነው የሳዑዲ ስታር ድርጅት ከያዘው አስር ሺ ሄክታር መሬት አምስት ሺ ሄክታር ተቀንሶ ወደ መንግሥት እንዲመለስ በማድረግ የክልሉን ወጣቶች ተጠቃሚ ለማድረግ እንደታቀደ ገልፀዋል፡፡ አቶ ኡሙድ በዚሁ ቃለ ምልልስ ‹‹ወደ አገር ውስጥ ከገቡ ፓርቲዎች መካከል የጋምቤላ ክልላዊ ንቅናቄና የጋምቤላ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ ይገኙበታል፡፡

እስከአሁን ግን ከብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጣቸው እውቅና የለም፡፡›› ብለዋል፡፡ በቀጣይነት ክልሉ ሙሉ በሙሉ ወደነበረበት ሰላምና ፀጥታ እንዲመለስ በትጋት እንደሚሰራም አስረድተዋል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=kk-bdasg-qA&t=158s

3 4
Previous Story

ዶ/ር አብይ ተፎካካሪ ፓርቲዎች 3 ወይም 4 እንዲሆኑ ጥሪ አቀረቡ

92789
Next Story

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የነዳጅ እጥረት ተከሰተ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop