November 10, 2018
3 mins read

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሃመድ አብዱላሂ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው በሰላም ተመለሱ

92455

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሃመድ አብዱላሂ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው በሰላም ተመለሱ::
የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን በትናንትናው ዕለት ከጎንደር የጀመሩት መሪዎቹ በባህር ዳር ከጠሚር ዶክተር አብይ አህመድ ጋር በመሆን በሶስትዮሽ ጉዳዮች ላይ ሲመክሩ ውለው ሀገራቱ የደረሱትን የሶስትዮሽ ስምምነት አፈፃፀም ላይ ተነጋግረዋል:: መሪዎቹ ከውይይታቸው በኋላ በሰጡት መግለጫ የኢኮኖሚ ትብብርና ቀጠናዊ ሰላምን የማስጠበቅ እቅድ በሚገባ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸዋል::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ “ከሁለት ወር በፊት በጋራ በነደፉት እቅድ አተገባበር ላይ ውይይት ሲካሄድ ነበር:: እቅዱ በተቀመጠው ልክ እየተተገበረ ይገኛል የሚል ድምዳሜ ላይ ተደርሷል::” ካሉ በኋላ ከሶማሌያ ፕሬዚዳንት ፈርማጆ ጋር በመሆኑ በኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን ማእቀብ ሊያነሳ መሆኑን “የማእቀቡ መነሳት የአከባቢውን ሰላም፣ ልማትና ትብብር እንደሚያሳድገውም በመግለጽ” በአድናቆት እንደሚያዩት ገልጸዋል::

በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ያሰራውን አዲስ ሆስፒታል ከሁለቱ መሪዎች ጋር መርቀው ከከፈቱ በኅውላ ለጥበበ ግዮን እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተመራቂዎች ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምሩቃኑ በተማሩበት ሙያ ስራ ከመጀመራቸው በፊት የሶስቱን አገራት ጥምረት ለማጠናከር ወደ ሶማሊያና ኤርትራ በመሄድ በሙያቸው ለጥቂት ጊዜ እንዲያገለግሉ ጥሪ ጥሪ አቅርበው በተማሪዎቹ ዘንድ አዎንታን አግኝተዋል:: በዚህም መሰረት ሃምሳ ሃምሳ የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ወደ ኤርትራና ሶማሊያ ተጉዘው ለተወሰነ ጊዜ የነፃ ህክምና በመስጠት እንደሚያገለግሎ ተገልጿል::
https://www.youtube.com/watch?v=ZvwwoqvPgSg

92452
Previous Story

መምህር ግርማ ወንድሙ በነጻ ተለቀቁ

92459
Next Story

በሌብነትና በሌሎች ወንጀሎች የሚፈለጉ የጦር መኮንኖች ታፈሱ | ልዩ ግብረ ኃይል ወደ መቀሌ አቀና

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop