November 10, 2018
2 mins read

መምህር ግርማ ወንድሙ በነጻ ተለቀቁ

92452

ዛሬ ለንባብ የበቃው ኢትዮጲስ ጋዜጣ መምህር ግርማ በነፃ መለቀቃቸውን ዘገበ። እንደጋዜጣው መምህር ግርማ ወንድሙ ነፃ የወጡት ከተከሠሡበት የወንጀል ክስ ነው። ለሶስት አመታት ከገንዘብ ማጭበርበር ጋር የተያያዘውን ጨምሮ ስምንት የተለያዩ ክሶች ቀርበውባቸው ፍርድ ቤት ሲመላለሡ ነበር ያለው ጋዜጣው ጥቅምት 28 ቀን 2011 ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ቀርበው ነፃ እንደተባሉ ገልፆዋል። በክሡ ምክንያት ከአገር እንዳይወጡ ተጥሎባቸው የነበረው የጉዞ እግድም ተነስቶላቸዋል ብሏል።

መምህር ግርማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርሥቲያን ዘንድ በአገልግሎታቸው የሀይማኖቱን ሥርአት የተከተሉ አይደሉም በሚል በተደጋጋሚ ነቀፌታ የሚቀርብባቸው መሆኑን ያወሣው ጋዜጣው ያስተምሩባቸውና ያጠምቁባቸው ከነበሩ እስጢፋኖስና የረር ሥላሤ ቤተክርሥቲያናት መታገዳቸውንም ጠቅሷል። እሥጢፋኖስ ቤተክርስቲያን በታገዱበት ወቅት በርካታ ተከታዮቻቸው “የፈውስ አገልግሎቶቹ ያናደዳቸውና በመምህሩ ተደማጭነት ቅር የተሠኙ የቤተክርስቲያኗ አመራሮች ናቸው በተንኮል ያስነሷቸው” በሚል ተቃውሞ ማሠማታቸውን ኢትዮጲስ አውስቷል።

https://www.youtube.com/watch?v=ZvwwoqvPgSg

92431
Previous Story

ኢትዮጵያ ስለምታቋቁመው የባህር ሃይል ማብራሪያ ተሰጠ | ጀነራል ብርሃኑ ጁላ ቤተመንግስት የሄዱት ወታደሮች ጉዳይም ተናገሩ

92455
Next Story

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሶማሊያ ፕሬዚዳንት መሃመድ አብዱላሂ የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው በሰላም ተመለሱ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop