November 6, 2018
4 mins read

ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አምባሳደሮችን ሾመ

የለውጥ እርምጃ እየሰራሁ ነው ያለው ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው እለት ለአምስት አምባሳደሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡ ሹመት የተሰጣቸው አምባሳደር ወይንሸት ታደሰ፣ አምባሳደር ማህሌት ኃይሉ፣ አምባሳደር ዶ/ር ቦጋለ ቶሎሳ፣ አምባሳደር ነጋ ፀጋዬ እና አምባሳደር ደዋኖ ከድር መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ጽ/ቤት ገልጻል፡፡ በሹመቱ መሰረትም፡-
አምባሳደር ወይንሽት ታደሰ የአፍሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች ጉዳዮች ቋሚ ተጠሪ
አምባሰዳር ማህሌት ኃይሉ የአውሮፓ፣ የአሜሪካ፣ የኤዥያ እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ቋሚ ተጠሪ፣
አምባሳደር በጋለ ቶሎሳ የዳያስፖራ እና ቆንስላ ጎዳዮች ቋሚ ተጠሪ
አምባሳደር ነጋ ፀጋዬ የኃብት ማኔጅመንትና አገልግሎት ቋሚ ተጠሪ
አምባሳደር ደዋኖ ከድር ደግሞ የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ጉዳዮች ቋሚ ተጠሪ ሆነዋል፡፡
አምባሳደር ወይንሸት በሲዊዲን አምባሳደር እንዲሁም በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የነበሩ ሲሆን አምባሳደር ማህሌት ኃይሉ ደግሞ በኒውዮርክ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቋሚ መልዕክተኛ ጽ/ቤት ምክትል የሚስዮን መሪ በመሆን ያገለገሉ ናቸው፡፡ አምባሳደር ዶ/ር ቦጋለ ቶሎሳና አምባሳደር ደዋኖ ከድር ደግሞ በኩባ አምባሳደር በመሆን ያገለገሉ ሲሆን አምባሳደር ነጋ ፀጋዬ አምባሳደርና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ዳይሬክተር ጄነራል በመሆንም ሰርተዋል፡፡

በኩዌት ኢትዮጵያዊትየቤት ሰራተኛዋን የገደለችው ሴት መከሰሷን ገልፍ ኒውስ ዛሬ ዘግቧል፡፡ ጋዜጣው በዘገባው ድርጊቱ የተፈፀመው አል ፌርዳውስ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ውስጥ መሆኑን ገልፆ፣ ተጠርጣሪዋ ዛሬ ፍርድ ቤት እንደቀረበችና ምርመራው እክሲጠናቀቅ ለ21 ቀናት እስር ቤት እንድትቆይ እንደተወሰነ አስረድቷል፡፡ የኩዌት አቃቤ ህግ በተጠርጣሪዋ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ግድያና ህገ ወጥ ሰው የማዘዋወር ክስ እንደመሰረተባትም ዘግቧል፡፡ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዳው ተጠርጣሪዋ በኢትዮጵያዊን በዱላ ደብድባ እንደገደለቻት ማስረጃዎች አሉ ብሏል፡፡ የተጠርጣሪዋ ጠበቃ ግን ደንበኛው ሆን ብላ ለመግደል አስባ ሳይሆን የቤት ሰራተኛዋን ለመቅጣት ብላ ባደረገችው ድርጊት ሁኑታው መፈጠሩን ገልፀው መከራከራቸውን ጋዜጣው አስረድቷል፡፡ የቤት ሰራተኛዋን ከደበደበቻት በኋላ ወደህክምና ቦታ ያልወሰደቻት ፖሊስንና እስርን በመፍራት እንደነበር ተጠርጣሪዋ ተናግራለች እንደዘገባው፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=0OBDIk-J-Do&t=71s

92384
Previous Story

በጎንደር እጃቸው የያዙት ቦምብ ይሰራል አይሰራም በሚል ሲከራከሩ ፈንድቶ አራት ሰዎች ሕይወታቸው አለፈ

92409
Next Story

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አርብ አማራ ክልል ናቸው

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop