ወ/ት ብርትኳን ሚዴቅሳ ወደ ኢትዮጵያ ልትገባ ነው

ታዋቂዋ እንስት ፖለቲከኛ ብርቱካን ሚደቅሳ ወደ በሚቀጥለው ሳምንት ወኢትዮጵያ እንደምትገባ ታወቀ:: ለረዥም ዓመታት በ እስር ላይ የቆየችው የቀድሞው በስድስት ኪሎና ፈረንሳይ አካባቢ የፓርላማ ተወዳዳሪና የፌደራል ፍርድ ቤት ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ ወደ ሃገር ቤት የምትገባው በዶ/ር አብይ አህመድ ግብዣ መሆኑ ታውቋል::

በአቶ መለስ ዜናዊ የስልጣን ዘመን የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛ በነበረችበት ወቅት የህጉን ክፍተት ተመልክታ የሕወሓቱን ባለስልጣን ስዬ አብርሃን ከፍርድ ቤት እንዲለቀቅ በመወሰን ባሳየችው ድፍረት የምትታወቀው ብርቱካን የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር፣ የአንድነት ፓርቲ መስራችና ሊቀመንበር በመሆን ለእስር በመዳረግ ከፍተኛ መስዋትነት ከፍላለች::

ከ እስር ከወጣች በኋላ በአሜሪካ ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪዋን የተቀበለችው ብርቱካን ከፖለቲካው ዓለም ራሷን አርቃ ሰንብታለች:: ብርቱካን በዶ/ር አብይ አህመድ ግብዣ የፊታችን ጥቅምት 28/2011 ከዋሽንግተን ዲሲ ተነስታ፤ ሐሙስ ጥቅምት 29/2011 ኢትዮጵያ እንደምትገባ ምንጮች ተናግረዋል::

ብርቱካን የአንዲት ሴት ልጅ እናት መሆኗ ይታወቃል::
https://www.youtube.com/watch?v=92rppGAN2Dk

ተጨማሪ ያንብቡ:  በአዲስ አበባ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ800 በላይ ቤቶች በመንግስት ፈርሰዋል

3 Comments

  1. Stolen from Entoto Forum for Social Justice blogspot

    News is being released practically every day that somebody from the diaspora is to visit the country on the invitation of the government – costs covered. As a project it is commendable no matter how much it costs – exorbitant for the country according some sources which the visitors theselves could have covered without much incovenience. This is not to question the approprieateness of Ms. Midekas’ invitation and visit. Obo G. Wolde is also in the country last week on a similar arrangement. We’re simply asking if there is any criteria the PM and his team use for the selection. If the criteria is known, ordinary citizens could make nominations for consideration by the PM. We mean like the Nobel Peace Price. Information if the invitees are expected to engage in any particlar type of work during their stay in the country other than polishing the image of the PM as benevolent leader and the government as friendly and receptive to dissidents might be helpful for the nomination. We would take the initiative to make a nomination. Mr. PM ! There are two people you cannot ignore : Ayte Gebremedehin Araya and Ayte Abreham Yayeh. Maybe you have their names already but we wouldn’t know until they set foot in tne country. Gebremedhin and Abreham have enormously contributed to the understanding of and resistance against TPLF rule by the Ethiopian people.)

  2. በአሜሪካ ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ደግሞ በሕዝብ አስተዳደር ሁለተኛ ዲግሪዋን የተቀበለችው Birkutan Mideksa (Ethiopia)
    Birtukan Mideksa will be the Eleanor Roosevelt Fellow with a joint appointment with W.E.B. Du Bois Institute. A former judge and the leader of Ethiopia’s Unity and Democracy for Justice Party, Birtukan was among opposition activists who were jailed for life after the disputed 2005 election. They were pardoned, but Birtukan was sent back to prison after the government accused her of violating the terms of the pardon. She was released in October 2010. At Harvard, she will work on the independence of the judiciary in closed societies. ሁለተኛ ዲግሪ?

  3. ሚደቅሳ! ያ! ብርቱ! ሚደቅሳ
    ታስረሽ፤ ተንገላተሽ፤ ተሰደሻልሳ
    ይበቃ ይሆን? ምሬቱ! ኣበሳ!
    ምን ለውጥ ኣለ? ምንስ ተነሳ?
    ይኖር ይሆን የተረሳ?
    ትቆዪ ይሆን? ወይስ ምልስ? ሆኖብናል ኣበሳ!
    ላንዱ የጣመው፤ ለሌላው ብስናት ቅርሻትሳ
    ጉድ! ጉድ! ለጉድ ነው! ሚደቅሳ!
    ፖለቲካችን ሊታይ ነው! በዳሰሳ!
    ኣደራ! እንደው ኣደራ! ትዘላብጂና! ጎረምሳ!!

Comments are closed.

Share