የብሔራዊ ቡድናችን ውጤታማ ጉዞ ተገታ

http://www.youtube.com/watch?v=ywVIyL7ALg4&feature=youtu.be
(ስፖርት አዲስ) ለብራዚሉ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ለማለፍ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው የመጨረሻ ማጣሪያ መጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ በሜዳዋና ደጋፊዋ ፊት ሽንፈትን አስተናገደች፡፡ የብሔራዊ ቡድኑ የዓለም ዋንጫ አስደናቂና ውጤታማ ጉዟ በናይጄሪያ ተገቷል፡፡
ዛሬ ከቀኑ በ10፡00ሰዓት የተደረገው የኢትዮጵያና ናይጄሪያ ጨዋታ በእንግዳው ቡድን ሁለት ለአንድ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ በጨዋታው ሦስቱ ግቦች ከዕረፍት መልስ የተገኙ ናቸው፡፡ ግብ በማስቆጠር ቅድሚያውን ወስዶ የነበረው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ነው፡፡ 56ኛው ደቂቃ ላይ በሃይሉ አሰፋ ከመስመር ለማሻማት የላካት ኳስ አቅጣጫዋን ስታ ግብ ልትሆን ችላለች፡፡ ለናይጄሪያ ሁለቱንም ጎሎች በ67ኛው እና 89ኛው ደቂቃ ላይ ኤሚኒኬ አስቆጥሯል፡፡ ኤሚኒኬ የመጀመሪያውን ከረዥም ርቀት ላይ አክርሮ በመምታት ሁለተኛውን በፍፁም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡
በጨዋታው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከዕረፍት በፊት በኳስ ቁጥጥር የተሻለ የነበረ ሲሆን አራት ያህል ሙከራዎችንም በሳላዲንና አዳነ አማካኝነት ማድረግ ችሎ ነበር፡፡ በተለይም ሳላዲን ካደረጋቸው ሁለት ሙከራዎች አንደኛዋ(24ኛው ደቂቃ ላይ ነው) የጎሉን መስመር ማለፍ ችሎ የነበረ ቢሆንም ዳኛው ሳያፀድቆት ቀርተዋል፡፡ በዚሁ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ናይጄሪያ በተመሳሳይ አራት ያህል ሙከራዎችን ማድረግ ችላ ነበር፡፡ በተለይም አንደኛዋ ኳስ ጎል መሆን ሲገባት በተጨዋቹ ስህተት ግብ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ከእረፍት መልስ የኢትዮጵያ ቡድን በተመሳሳይ በኳስ ቁጥጥርና ግብ በማስቆጠር የበላይነቱን ማስጠበቅ ችሎ ነበር፡፡ ይህ ግን የሆነው እስከ 67ኛው ደቂቃ ብቻ ነው፡፡ 67ኛው ደቂቃ ላይ ናይጄሪያ በኤሚኒኬ የአቻነት ጎል ማስቆጠር ከቻለች በኋላ የበላይነቱን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ችላለች፡፡ በ89ኛው ደቂቃ ላይም አይናለም ሃይሉ በአቋቋም ችግር ምክንያት በፈፀመው ስህተት ዳኛው የሰጡትን ፍፁም ቅጣት ምት ኤሚኒኬ አስቆጥሯ ጨዋታው በናይጄሪያ ሁለት ለአንድ አሸናፊነት ሊጠናቀቅ ችሏል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የፖለቲካ እስረኞችን የመፍታቱ ጉዳይ አሁንም እያወዛገበ ይገኛል

ኢትዮጵያ በሜዳዋ ባደረገችው ጨዋታ አራት ያህል ቢጫ ካርዶች ታይተዋል፡፡ ሁሉንም ካርዶች የተመለከቱት ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ተጨዋቾች ናቸው፡፡ ስዩም ተስፋዬ፤አዳነ ግርማ፤አዲስ ህንፃና አይናለም ሃይሉ ናቸው፡፡ የዛሬውን ጨዋታ የመሩት ካሜሮናዊው ዳኛ በ24ኛው ደቂቃ ሳላዲን ሰይድ ያስቆጠረውን ጎል ባለማፅደቃቸው ከተመልካቹ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ያደረገው ውጤታማ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጉዟ ዛሬ በተመዘገበው ውጤት ምክንያት የተገታ ይመስላል፡፡ ቡድኑ ከአንድ ወር በኋላ በሚኖረው የመልስ ጨዋታ በሁለት ግብ ልዩነት ማሸነፍ ከቻለ የማለፍ ዕድል ይኖረዋል፡፡ ይሁን እንጂ ናይጄሪያን በሜዳዋ በወሳኙ ጨዋታ ማሸነፍ ከባድ የሚሆንበት ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ቡድን በዚህ የዓለም ዋንጫ ከአራት ሀገሮች ጋር ባደረገው የማጣሪያ ጨዋታ አንድም ጨዋታ አልተሸነፈም ነበር፡፡ ይህም ጉዟ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ የመጀመሪያውና ውጤታማው ነበር፡፡ በአምስተኛውና የመጨረሻው ማጣሪያ ጨዋታ ግን በናይጄሪያ ያውም በዚህ ሁለት ዓመት አንድም ጊዜ ባልተሸነፈበት ሜዳ ሊሸነፍ ችሏል፡፡

ምንጭ፡ ስፖርት አዲስ ጋዜጣ

3 Comments

  1. I’m glad the Ethiopian team is out of the Brazil scope. I saw the team’s performance and we are way too behind both psychologically and in competency to represent Africa at a World class level. I haven’t seen any serious danger caused by the Ethiopian team that frustrated the Nigerian defense. And the people never dare to criticize Ethiopia’s 32 years of football trauma as we tend to say “they played well” instead of “we lost” and ask “why??”

    • I am not glad for Walia’s loss. Who on earth is going to be glad when their country national tem loses the game? No body. Soccer is unpredictable. How about when Maradona’s Argentina team with players like Messi lost 4 to 0 against Germany last time? It is just an event of that day that Argentina lost that particular game. Another match even the next day could have the opposite result. Probably I would agree in terms of tactical setup to be improved. Btw. Walya is right now one of the 10 best candidates to represent Africa to Brazil, better than the rest of 40 African teams coming into spotlight of international soccer. This is huge by itself for Ethiopia.

  2. It is not over yet. we have nothing to lose but everything to gain. we will play 110% and go through to the world cup.

Comments are closed.

Share