March 22, 2017
1 min read

በሳንጃ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ በተወረወረ ቦምብ 6 ሰዎች ቆሰሉ | ከፋኝ ጦር አስተዳዳሪው ቤት ላይ የቦምብ ጥቃት አደረሰ

ከሙሉነህ ዮሐንስ

ጎንደር ሳንጃ ከተማ በውጥረት ውስጥ እንደምትገኝ ተዘገበ:: ላለፉት ጥቂት ቀናት በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የሰነበተችው ሳንጃ ከተማ ውስጥ ከሕወሓት መንግስትና በኩልም እንዲሁም ከከፋኝ ጦርም ጥቃቶች ተሰንዝረዋል::

አርማጭሆ ሳንጃ ከተማ በ12/07/09 ከምሽቱ 3፡09 ሰዓት በከፋኝ ጦር ወደ ከተማዋ እያሱ ይላቅ ቦንብ አስተዳዳሪው ቤት ተወርውሮ ጉዳት ማድረሳቸው ተዘግቧል:: የከፋኝ ሃይሎች የጀግናው ጎቤ መልኬ ደም በከንቱ ፈሶ አልቀረም ጥቃቱ ተጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸው ታውቋል።

በጥቃቱ የተበሳጨው ወያኔ ከፋኞችን ከህዝብ ለማጣላት በንግድ ባንክ ላይ ፈንጅ ጥቃት እንደሰነዘረ ጥብቅ መረጃ ደርሶናል። እማኞች እንደጠቀሱት በተመሳሳይ ቀን ሳንጃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ በተወረወረ የወያኔ ቦንብ ጥቃት ስድስት ሰዎች ቆስለው በአሁኑ ሰዓት ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛሉ።

ሳንጃ ከተማ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ትገኛለች::

Previous Story

በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አሳሳቢ ሆኗል | ከግማሽ በላይ የመንግሥት ሠራተኞች ትክክለኛ የትምህርት ማስረጃ የላቸውም

Next Story

የዳዊት ጠጠር! (መብራቱ ከስቶክሆልም)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop