የጭለማ ዘመን ከኢትዮጵያ ማህጸን ደጋግሞ የመፍለቁ ሚስጢር ምን ይሆን?

ሸንቁጥ አየለ
—————-
-ዘመነ መሳፍንት ኢትዮጵያን 179 አመታት በጨለማ ዘመን ዉስጥ አስሮ አኖራት::በርካታ ሀገራት በተለይም ምዕራባዉያን ወደ ቀጣይ እድገት የተሸጋገሩበትን የግንዛቤ ለዉጥ የጨበጡት እና መሰረታዊ የአስተሳሰብ ለዉጥ ያመጡበት ወቅት ይሄዉ ኢትዮጵያ በዘመነ መሳፍንት ጨለማ ዉስጥ ስትዳክርበት የነበረዉ ዘመን ነዉ::

-ኢትዮጵያ በታላቁ አጼ ቴዎድሮስ ራዕይ እና ተጋድሎ በዳግማዊ አጼ ሚኒሊክ የማግባባት ጥበብ እንደ ሀገረ ከተሰባሰበች ብኋላ ከማህጸኗ የሚፈልቀዉ አስተሳሰብ አሁንም ወደ ጨለማ ዘመን የሚጎትታት ሆኗል::ህዝቡን እንደ ዘመነ መሳፍንት በብዙ ንጉሶች እና ገዥዎች ለመቀጥቀጥ እና ሀገሪቱን ለመበተን የሚጮህ ከፉ መንፈስ ጉልበት ያገኘ ይመስላል::


-የኢትዮጵያን ህዝብ እግዚአብሄር ኢትዮጵያ ብሎ የጠራዉ አንድ ህዝብ ነዉ::መልኩ እና መልከዓምድሩን ባህሪዉን እና ማንነቱን ሁሉ መጽሀፍ ቅዱስ ዘርዝሮ የዘገበለት ህዝብ ነዉ:: ሆኖም የኢትዮጵያ ምሁር እና ፖለቲከኛ ተብዬዉ ኢትዮጵያዊነትን እንኳን በተባለዉ ደረጃ ሊያከብረዉ ቀርቶ በኢትዮጵያዊነቱ ላይ ነጋ ጠባ እንደተጨቃጨቀ ይሄዉ አመታታ አለፉ:: አንዱ ጎሳ ከሌላዉ ጎሳ የተለዬ እንደሆነ የሚሰብኩ እና ጥላቻን የሚዘሩ ፖለቲከኞች ምድሪቱን ቀስፈዉ ከያዟት ይሄዉ 50 አመታት አለፋቸዉ:: ወደ ፊት በማዬት የነገን የጋራ በረከት ብሎም በመላዉ አለም እየፈለቀ ያለዉን የቴክኖሎጂ ጸጋ ህዝባቸዉ እንዲጠቀምበት ከማድረግ ይልቅ ኢትዮጵያዉያን ለታላቅ የመጠፋፋት መንፈስ እንዲነሳሱ ልዩነት እና ጥላቻን ሰባኪ በዝቷል::


-ቢልጌት እና ታላላቅ የምድራችን ተጽእኖ ፈጣሪዎች እንደሚተነብዩት የሰዉ ልጅ በ2025 ዓም አጠቃላይ የህይወት እንቅስቃሴዉ በቴክኖሎጂአዊ ቀመር በእጅጉ ይለወጣል:: ይሄ የሚሆነዉ ታዲያ አሁን በቴክኖሎጂዉ ላይ በጥልቀት ሳያሰልሱ እየሰሩ ባሉ ህዝቦች እና ሀገራት ዘንድ ነዉ::

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኃይለማርያም ደሳለኝ ቁልቁለቶች - ከተመሰገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)


-ኢትዮጵያስ? የኢትዮጵያ ጉዳይ እማ አሁንም ወደኋላ መጎተት ሆኗል::ቴክኖሎጂ ላይ መስራት እና ከቴክኖሎጂ ጋር ህዝቡ መተዋወቁ ቀርቶበት የሚግባባበት የጋራ ሀገር; የጋራ መንፈስ እና ቃላት እንኳን አጥቷል::አሁን ያለዉ ትዉልድ እርስ በርሱ ሊግባባ ቀርቶ ቀድመዉ ከነበሩ የታሪክ ተዋንያን ጋርም ተጣልቷል:: የተሰራለትን ሀገር በምስጋና ተረክቦ የተሻለ ዲሞክራሲያዊ ሀገር አድርጎ ለመስራት በመግባባት ከመስራት ይልቅ ሀገሩን በመከራ ዉስጥ አልፈዉ የገነቡ አባቶችን ምላሱን እያወጣ መሳደቡን ቀጥሏል::የሰፈነዉ ሀገራዊ መንፈስ እጅግ አስጨናቂ እና አስፈሪ ነዉ::


-ይሄን ያስተዋለ እና ጭቅጭቅ የሰለቸዉ አንዳንድ ሰዉ ታዲያ አብረን መኖር ካልሆነልን ለምን አንለያይም ሲል ሀሳብ ያቀርባል:: ግን ጥያቄዉ የኢትዮጵያ ሰዉ ቢለያይስ አሁን በሀገር ደረጃ ያለዉ የመለያዬት እና የጥላቻ መንፈስ ወደ እዬ ነገዱ አይወርድም ወይ? ደግሞስ እዉነት ለመለያዬት ኢትዮጵያኖች ቢወስኑ እርስ በርስ የሚያጫርሳቸዉ ብዙ ነገር የለም ወይ? አንዳንዱ እንደሚያስበዉ እያንዳንዱ ቁራጭ መሬት እያንጠለጠለ መሮጥ ይቻላል ወይ? ይሄኛዉ መሬት የዚያኛዉ ጎሳ/ነገድ ብሎ እርኩስ መንፈስ የሰፈረበት ወያኔ እንደከለለዉ ሀገሩ ሲፈርስ ህዝቡ ተስማምቶ ይሄ የኔ ያኛዉ ያንተ ብሎ ምድሪቱን መከፋፈል ይችላል ወይ?መለያዬትስ አብሮ ከመኖር ቀላል ነወይ? ከቶስ ኢትዮጵያ ብትፈራርስ አትራፊ ወገን አለ ወይ? አሁን ነገር እና ጥላቻ የሚጎነጉነዉን ፖለቲከኛ እና ምሁር አብሮ መኖር ያላስማማዉ መለያዬት ሊያስማማዉ ይችላል ብሎ ማሰብ ይቻላል ወይ?


ዋናዉ ጥያቄ ግን እንዲህ የጭለማ ዘመን ከኢትዮጵያ ማህጸን ደጋግሞ የመፍለቁ ሚስጢር ምን ይሆን?

1 Comment

  1. MInmistir alew. The zemene Mesafint was the dark age in Ethiopia. These 25 years with TPLF now in power are also the darkest ages in Ethiopia again. Both are began by the Tigreans. The Zemene Mesafint was began by Michael Suhul, a Tigrean who ascend to power poisoning his allies, and foes. He led Ethiopia into disarray, which took about 800 years to bring back the entire state into unified administration.
    There is no secret about it when the dark ages come to Ethiopia. Question to the writer: What do you think the solution for this will be? Just precisely ok. Why shoudl Ethiopia put in such a shame by groups who came to power from that region?

Comments are closed.

Share