September 1, 2013
2 mins read

የፌደራል ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ደበደበ፣ ተቃውሞ ሰልፉን አደናቀፈ

ከርእየ- ሁለንተና ከአዲስ አበባ
ዛሬ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ. ም ሠማያዊ ፓርቲ በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ገዥው ፓርቲ ለማደናቀፍ ከፍተኛ ውዥንብር፣ ድብደባና ሁከት ፈፀመ፡፡ ከ3 ወር በፊት ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ. ም ባደረገው የተቃውሞ ሰልፍ፡- ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ የሀይማኖት ተወካዮች፣ በግፍ የታሰሩ ዜጎች ባስቸኳይ እንዲፈቱ በስብሰባው ያሳወቀ ሲሆን ምላሽ ባለማግኘቱ ነው ሰልፍ የጠራው፡፡
ይሁንና ገዥው ፓርቲ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሚል መልምሎ ባስቀመጣቸው ካድሬዎቹ አማካኝነት የተቃውሞውን ስብሰባ ያደናቀፈ ሲሆን በ25/12/05 ዓ. ም ምሽት ወታደሮቹን ልኮ በቢሮው ውስጥ የነበሩትን አመራሮችና ደጋፊዎችን ደብድቧል፡፡ አቶ ማርቆስን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ክፉኛ ተደብደበው በ5 እስር ቤቶች ከፋፍሎ ካሰረ በኋላ ከምሽቱ 5፡00 ፈቷቸዋል፡፡ ኢንጅነር ይልቃልም ታስረው ተፈተዋል፡፡ ዛሬ ጠዋት 12፡ 00 ጀምሮ በጽ/ ቤቱ ከፍተኛ ቅስቀሳ የነበረ ሲሆን ወታደሮች በህገ ወጥ ገብተው በማስቆም ፖስተሮችን በመቅደድ፣ ጀኔሬተሮችን በመቀማት፣ ከፅ/ ቤታቸው እንዲወጡ አድርገዋል፡፡
በአንጻሩ በሀይማኖት ተቋማት ስም የጠራው ስብሰባ፡- እድሮች፣ የቀበሌ ነዋሪዎች፣ የቀጠና ካድሬዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ያደራጃቸው፣….በሎንችና፣ በአዜብ ቀንዶ፣ በአሮጌ አውቶቡሶች በመጓጓዝ መስቀል አደባባይ ከተገኙ በኋላ ያለምንም ተልእኮ ተበትነዋል፡፡ አብዛኞቹ በእግራቸው ተመልሰዋል፡፡ አላማው የሰማያዊ ፓርቲን የተቃውሞ ሰልፍ ማደናቀፍ ብቻ ነበር፡፡
ይህ የገዥው ፓርቲ ግፍ በዜግች ላይ ከፍተኛ ቁጣና እምቅ እልህ አንደሚፈጥር ታውቋል፡፡

6946
Previous Story

የአባይ ቦንድ ሽያጭ በጉተምበርግ ከሸፈ፤ ድብድብ ተነሳ (Video)

Muslim Etiopia 1
Next Story

በዛሬው ሰልፍ ላይ ከወጡት መካከል ከ200 በላይ ሙስሊሞች ታሰሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop