October 4, 2016
2 mins read

በእሬቻ በአል በተወሰደው ግፋዊ እርምጃ ላይ የተለያዩ ከተሞች እና ከፊል አዲስ አበባን ጨምሮ የተቃውሞ አሰሙ በወያኔ ንብረቶች ላይ እርምጃ ወሰዱ።

(ዘ-ሃበሻ)በእሬቻ በአል ላይ በጨካኙ የወያኔ ሰራዊት የተፈጸመው ህዝባዊ ተቃውሞ በጃሞ የተነሳው ተቃውሞ በተለያዩ የኦሮሚያ እና የአዲስ አበባ ክልሎች እየተዛመቱ መምጣቱ ተገልጦአል ። በአዲስ አበባም የተለያዩ የንግድ ሱቆች ተዘግተዋል ። በሌሎችም ቦታዎች የኦሮሞ ተወላጆችም ሆኑ ሌሎችም ዜጎች በህብረት የኦሮሞ ህዝብ ነጻ መሆን አለበት ግድያ ይቁም ፣ወያኔ ከስልጣን ይውረድ በማለት ከፍተኛ ድምጽ በማሰማላት ላይ ይገኛል ።
በአለም ገና ሞጆ ፣ቡራዩ እና ሌሎችም ቦታዎች ከፍተኛ ንቅናቄ ከመታየቱም በላይ በአሸዋ ሜዳም ከፍተኛ ሃይል ያለው ህዝብ ወደ ከተማ በመግባት የተለያዩ ድምጾችን አሰምቶአል ፣መንገዶችም ተዘግተዋል ። የትራንስፖርት አገልግሎቶች የቆሙ ሲሆን የአጋዚ ጦርም በተለያዩ ቦታዎች ተሰግስገው የገቡ ሲሆን በአንዳንድ ቦታውችም በንጹሃን ዜጎች ላይ ከፍተኛ እርምጃ እየወሰዱ ይገኛሉ ።
ትምህርትቤቶችም በጊዜ የተዘጉ ሲሆን በሰሜን ሸዋ በሰላሌ አካባቢ ህዝቡ በአደባባይ ከገበሬው ጋር በመተባበር ወደ አደባባይ ወጥተዋል ። በሌሎች ገጠር ከተሞች ከፍተኛ እንቅስቃሴ ቀጥሎአል ተቃውሞው በሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች እንደሚዛመት ምንጮቻችን ገልጸዋል ።

Previous Story

ለዘብተኞችን ማጥቃት፤ አክራሪዎችን ማብዛት -አንዱዓለም ተፈራ

67025
Next Story

<<እነሱን እንቅልፍ የሚነሳቸው በተለይ የኦሮሞና አማራው ተስማምቶ አንድ ላይ ለመብቱ መቆም ነው>>አባ ጫላ ለታ የኦነግ ውጭ ጉዳይ ሀላፊ (በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop