September 28, 2016
1 min read

የጅምላ እስርና ግድያ እየፈጸሙ ያሉ የህወሃት/ኢህአዴግ ባለስልጣናት ለፍርድ እንዲቀርቡ ተጠየቀ

TPLF Ethiopian Leaders

ኢሳት (መስከረም 17 ፥ 2009)
በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ግድያና ጅምላ እስር እየፈጸሙ ያሉ ባለስልጣናት ሆነ የጸጥታ ሃይሎች ለፍርድ እንዲቀርቡ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች አንድነት ጠየቀ።
አለም አቀፍ ህብረት ለኢሳት በላከው መግለጫ ህዝብን ማገልገል የሚገባው መንግስት ዜጋውን እየጨፈጨፈ መቀጠል ስለለለበት ስልጣንን መልቀቅ ይኖርበታል ብሏል።
ከዚህ በኋላም የሚፈጸም ግድያና ጅምላ እስር በአስቸኳይ እንዲቆም አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዕምነት ተከታዮች አንድነት በመግለጫው ጠይቋል።
ህብረቱ ለኢትዮጵያ ህዝብን የሚያገለግሉና በዕውቀት የሚሰሩ መሪዎች እንድሰጣት ሁሉ በጸሎት እንዲተጋና ህገወጥ ድርጊቶችን እንዲያወግዝ ጥሪን አቅርቧል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መዋቅርና ሃብቷ በዘር ሃረጋቸውን በፖለቲካ አቋማቸው ከገዢው ፓርቲ ጋር በወገኑ ሰዎች እየተበዘበዘ መሆኑን ህብረቱ ለኢሳት በላከው መግለጫ አብራርቷል።

Previous Story

(ኢሳት) በጎንደር እድገት ፈለግ ወይም አሽዋ ሜዳ ከተባለው ቦታ ቁጥራቸው ያልታወቁ የመከላከያ ሰራዊት አባላት መጥፋታቸው ታወቀ፡፡

timthumb.php
Next Story

ጉዞአችን ወዴት ነው?( ሉሉ ከበደ)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop