የኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌስቲቫል በሰሜን አሜሪካ ነገ በሜሪላንድ በድምቀት ይጀመራል

(ዘ-ሐበሻ) ዓመታዊው የኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌስቲቫል በሰሜን አሜሪካ ነገ እሁድ ጁን 30 ቀን 2013 ዓ/ም በደመቀ ሁኔታ እንደሚከፈት ታወቀ። ከተመሠረተ 30ኛ ዓመቱን የሚደፍነው የኢትዮጵያ ሰፖርትና የባሕል ፌደሬሽን በሰሜን አሜሪካ(ESNFA) ከሰሜን አሜሪካና ከተለያዩ የዓለም ክፍል የሚመጡ ወገኖች ዝግጅቱን ይታደሙታል ተብሎ እየተጠበቀ ነው።
ኢትዮጵያውያኑን በአንድነት እያሰባሰበ ላለፉት 30 ዓመታት የቆየው ይኸው ፌዴሬሽን በዚህ ዓመትም የተሳካ ዝግጅት ያከናውናል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። ይኸን ተከትሎ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ወ/ማርያም ባስተላለፉት መልዕክት “ፈደሬሽናችን ውስጣዊ ችግር በአጋጠመው ወቅት ያገባናል በማለት የተባበሩን የመገናኛ ብዙሃንን ምስጋና እናቀርባለን” ብለዋል። የቀድሞው ፕ/ት ሙሉ መልዕክት የሚከተለው ሲሆን ዘ-ሐበሻ ይህን የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል ለአንባቢዎቿ ከመክፈቻው እስከ መዝጊያው በተከታታይ የምትዘግብ መሆኗን ትገልጻለች።

የ ኢትዮጵያ ሰፖርትና የ ባሕል ፌደሬሽን በሰሜን አሜሪካ(ESNFA) ከሃይማኖት ከጎሳ ከፖለቲካ ልዩነት የነፃና ለትርፍ ያልተቋቋመ ህዝባዊና ኢትዮጵያዊ ሰውነት ያለው ድርጅት ነው፡፡ ይህ ድርጅት ላለፉት 30 ዓመታት ኢትዮጵያውያንን በማሰባሰብና በማገ ናኘት ሕፃ ናትንና ወጣቶችን የ ኢትዮጵያን ወግ፤ ልማድና ባሕላቸውን እንዲያውቁ የረዳ፡፡ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ከወጡ ረዥም ጊዜ ላስቆጠሩ ኢትዮጵያውያኖች ከዘመድና ከወዳጆቻቸው ጋር መገናኛ መድረክ መሆን የቻለ አንጋፋ ድርጅት ነው፡፡ የበአሉ ሣምነት ጁላይ 4 የአሜሬካ የነፃነት በአል ማክበሪያ ሳምንት በመሆኑ (July 4th weekend Amercan Independence Day)ይህቺን ሁለተኛ ሀገ ራች፡ የ ሆነ ቺውን የአመሪካንን፡ የነፃነት፡ በዓል ከተቀረው አሜሪካውያን ጋር እንድናከብር አ ድር ጎ ና ል፡ ፡

ፈደሬሽናችን ESFNA ካሉት ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች አንኳሮቹ፡-

በየስቴቱ ያሉ ኢትዮጵያኖችን በያሉበት አካባቢ ሆነው የስፖርት ቡድን በማቋቋምና እነ ዚህም ቡድኖች በኢትዮጵያውያን አሰልጣኞችና ቡድን መሪዎች ተደራጅተው ለውድድር እራሳቸውን ማዘጋጀት ሲሆን የቡድኑም አባለት፤ አላማ ወጣቶቹ ሙሉ የኢትዮጵያዊነት መንፈስን የተላበሰ የቡድን ስሜት ኖሯቸው ዝግጅቱን ኢትዮጵያዊ ስሜት እንዲኖረው በማድረግ የወከሉትን ቡድን ወይንም ስቴት ለውጤት ማብቃት ሲሆን ይህም ለአንድ ሳምንት ተወዳዳሪ ቡድኖች በደረጃ የሚለያዩበት ነው፡-

ሌላው የኢትዮጵያ ቀን፡ሲሆን፤ በዚህ ዝግጅት፤ በጁላይ 4 ቀን የስቴቱንና የከተማይቱን ባለስልጣኖች በመጋበዝ የኢትዮጵያን ታሪክ የብሔር ብ ሔረ ሰ ቦ ች ን ባ ሕ ል ና ወ ግ የ ሚያ ስ ተ ዋ ውቅ ል ዩ ድ ራ ማዊ ት ዕ ይ ን ቶ ች የ ሚቀ ር ብ በ ት እንዲሁም ሕፃናት የተለያዩ በሕላዊ ትርዕቶችንና መዝሙሮችን የሚያሳዩበት ባጠቃላይ የሀገራችንን መልካም ገጽታ የሚያሳዩና የሚያስተምሩ ዝግጅቶችን በማቅረብ የታደሚውን የሀገር ስሜት መቀስቀሻ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያውያንን፤ በየትም ሀገር ቢሆን የሚያኮራና የሚያስከብር ጥሩ ቀለም ያለው የወግና ልማድ እንዲሁም የታሪክ ባለቤት መሆናችንን የምናሳይበት የዝግጅታችን ዋና አካል ነው››

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 49 (Zehabesha Newspaper # 49) - PDF

ESFNA በሜዳው ውስጥ ከሚከናወነው ፕሮግራም በበለጠ ለበአሉ ድምቀት የሚሆኑ ከሜዳውውጭ የሚከናወኑትትእይንቶችሲሆኑ እነዚህምግለሰቦች በቡድንምሆነ በተናጥልሆነውከፌዴሬሸኑበሚከራዩትድንኳንውስጥለህዝቡ የሚያቀርቡት የተለያዩ አገልግሎቶች ሲሆኑ ከነዚህም በጥቂቱ የተለያዩ ኢትዮጵያ ስም ያላቸው የባህል የምግብ ቤቶች የባህላዊ የስጦታ እቃዎች፤የኢትዮጵያ ሙዚቃ መደብሮች የተለያዩ ኢትዮጵያዊ ዲዛይነሮች የሰሯቸው የሀገር ባህል አለባሳት መሸጫ ሱቆች የመፅሃፍት መደብር ወዘተ… እነዚህን የተለያዩ ፕሮግራሞች ለመሳተፍ የሚመጣው ኢትዮጵያዊ ሁሉ የኢትዮጵያዊ ጨዋነት በተላበሰ ሁኔታ ምንም አይነት እረብሻና ብጠብጥ ሳይኖር ሳምንቱን ሙሉ ለጥበቃ የተቀጠሩትን በሊሶች ባስገረምና ባስደነቅ ሁኔታ በሰላም የሚያሳልፉበት ትንሺቷን ኢትዮጵያ የምናይበት የ ESFNA አካል ነው፡፡

ESFNA ከላይ ከተጠቀሱት የንግድ ድርጅቶች ጎን ለጎን ለሃይማኖት ተ ቐ ማት ና ለ እ ር ዳ ድ ጅ ቶ ች ያ ለ ክ ፍ ያ ቦ ታ በ መስ ጠት አ ላ ማቸ ውን እንዲያስተቃውቁ ያደርጋል ፡፡

ESFNA በዝግጅቱ ከሚያካትታቸው ፕሮግራሞች ሌላኛው በየ አመቱ በሚያደርገውዝግጅት ላይ የክብር እንግዶችን መጋበዝ ሲሆኑ እነዚህም በተለያዩ ስራ ዘርፍ ላይ ተሰማርተው ለኢትዮጵያ ባደረጉት አስተዋጽኦ ትልቅ ቦታ የምንሰጣቸው ገለሰቦች ናቸው፡፡ ከእነዚህም በጥቂቱ ቀደም ባሉት አመታት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገት ትልቅ አስትዋፅኦ ያደረጉ፤ በኦሎምፒክና በዓለም አቀፍ የ ሰፖርት ውድድሮች ላይ የ ኢትዮጵያን ሰንደቅዓላማ ከሌሎች በልጦ እንዲውለበለብ የደረጉ ስፖርተኞች እንዲሁም ፌደሬሽናችን እያደገና እየተጠናከረ ሲመጣ ሃሳቡን ሰፋ በማድረግ ሌሎች ባለውለታ ባለሞያዎችን ማለትም በተለያዩ ሥራዎች በአለም አቀፍ ዝግጅት ላይ ተሳትፈው የኢትዮጵያን ስም ያስጠሩ፤ የታሪክ ተመራማሪወችና ደራሲዎች ሳይኒስቶችና በማሕበራዊና በበጎ አድራጎት ሥራ ከፍ ያለ ተሰትፎ ያደረጉ ግለሰቦች፤ አርቲስቶችና የሙዚቃ ባለሞያዎች የመሳሰሉትን ሲሆን የዚህ ፕሮግራም ዋናኛ አላማ እነዚህን ኢትዮጵያውያን ከህዝቡ ጋር ማስተዋወቅና እርዳታ ለሚያስፈልጋቸ የገንዘብና የቁሳቁስ ስጦታዎችን መለገስ ሲሆን በተጨማሪ ለወጣት ኢትየጵያውያን የሃገራቸው ታላላቅ ሰዎች መልካም ተግባር አስተምሮ ለማለፍም ነው፡፡

በዚሁ 30 ዓመታት ውስጥ ቁጥራቸው ከሚሊዮን የሚበለጡ ኢትዮጵያውያንንና የኢትዮጵያን ወዳጆቻች፤ ከማስተናገዱም በላይ በሺዎቹ የሚቆጠሩ የንግድ ደርጅቶችን አሳትፏል፡ ፡ ቁጥራቸው በዛ ያሉ የ ኪነ ጥብብ አርቲስቶችን ሥራ ፈጥሯል፤ዝግጅቱ በሚደረግባቸውከተማዎችለሚገኙየኢትዮጵያውያንየንገድ ድርጅቶችና በከተማው ውስጥ ላሉ ሆቴሎችና የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ በየዓመቱ አሰገብቷል፡ ዝግጅቱ በሚደረግባቸው ቦታዎች የስቴቱንና የከተማውን የመንግስ በለስልጣናት በመጋበዝ በስቴቱ ውስጥ የሚኖሩት የኢትዮጵያውያን ብዛት በማሳየት ለስቴቱም ሆነለከተማውተመራጭተወዳዳሪዎችቀልብየሚስብ ኢትዮጵያውያንንብዛት በ ማሳ የ ት በ ምር ጫው ላ ይ ኢት ዮ ጵ ያ ውያ ን ለ ውጥ ማምጣት እ ን ደ ሚች ሉ አሳይቷል፡ ፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሚኒሶታውን ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ በማስመልከት በKfai Radio የተሰጡ የሕዝብ አስተያየቶች

ESFNA እንደ ኢትዮጵያዊ በጎ አድራጎት ድርጅት ኢትዮጵያውያንን በአመት አንዴ ከማሰባሰብ ውጪሃገራችን በተለያየ ጊዜ ባጋጠማት ችግሮች እርዳታ ያደረገ ሲሆን ይኸውም ህዝባችን በርሃብ በጎርፍ አደጋ ሲጎዳ ፤ በኤች. አ ይ . ቪ . ወ ላ ጆ ቻ ቸ ውን ላ ጡና ወ ላ ጅ አ ል ባ ለ ሆ ኑ ህ ጻ ና ት መር ጃ የሚውል ገንዘብ ወደ ሃገር ቤት በመላክ እንዲሁም ወጣቶችን በውጤታቸው በማወዳደር የከፍተኛ ት/ቤት ክፍያ የገንነዘብ ድጎማ መስጠትና የመሳሰሉት ይገኙበታል …

ESNFA እንግዲህ በዚህ የ30 አመታት ጉዞ ውስጥ ለሰራቸው በጎ ተግባራት ሁሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን ከተለያዩ የአሜሪካን ስቴቶች ለስፖርት ውድድር ዝግጅቱ ላይ መገኘትና የህዝቡ ድጋፍና ተሳትፎ በዋናነት ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዝ ሲሆን በመቀጠልም በየአመቱ በገንዘብም ሆነ በነ ጻ አገ ልግሎት በመስጠት ለፌዴሬሽናችን እዚህ መድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉልንን ግለሰብና ድርጅቶችን ማመስግ ተገቢ ነው፡፡

የክብር እንግዶቻችን ሁሉ ጥሪያችንን አክብው በበአላችን ላይ በመገ ኘታቸው፤
የ ኢትዮጵ አየ ር መንገ ድ ለአለፉት 25 ዓመታት ለክብር እንግዶቻችንና በሎተር እጣለታዳሚውየሚሰጡነፃ የማጓጓዣየአየር ትኬቶች በመስጠት
በተለያዪ ጊዜያቶች ፈደሬሽናችንን ስፖንሰር በማድረግ ከአንድ ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ ገንዘብ በመለገስና በክብር እንግዳነት ለጋበዝናቸውን ታሪክ ሰሪዎች ገንዘብና ሥራ በመስጠት የተባበሩንን 2002 ዓ.ም የክብር እንግዳችን ሼህ መሐመድ አሊ አላሙዲን፤
ላለፉት 15 አመታት ስፖነሰር ያደረገንን የዌስተርን ዩኒየንን
የሰንሻይን ሪል ስቴት፤ የጊፍት ሪል ሰቴትና ሮዜታ ሪል ሰቴትን
ስታድዮሙ ውስጥ ቦታ በመከራየት ከፍተኛ የገቢምንጭ ከመሆናቸውም በላይ ዝግጅቱ የ ተሟላ እንዲሆን የ ረዱንና የ ተባበሩንን የ ተለያዩ የ ንግድ ድርጅቶች
እንዲሁም የተለያዩ ባሕላዊና ዘመናዊ የሙዚቃ ባንዶችና ሙዚቀኞችና በግል የ ተባበሩንን አርቲስቶች
ፈደሬሽናችን ውስጣዊ ችግር በአጋጠመው ወቅት ያገባናል በማለት የተባበሩን የመገናኛ ብዙሃንን
ለአለፉት 30 ዓመታት ከየስቴቱ ክለባቸውን በመወከል ኮሚቴ አወቅረው የቦርድ አባል በመሆን ከማህላቸው የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አደራጅተው ይህን ከፍያል ሀለፊነት ከየክለቦቻቸው በአደራ ቃል ኪዳን ተረክበው ዲሞክራሳዊ አሠራር በተሞላበት፤ ግልርጽነ ትና ተጠያቂነ ት አስፍነ ው ብዙዎች ለዓመታት ጊዛቸውንና ገንዘባቸውን ሰውተው አንዳንዴም ትዳራቸውንን ቤተሰቦቻቸውን አሰጨንቀውደከመኝ ሰለቸኝ ሳየሉ የሕዘብን እሮሮ ችለው ፈደሬሽኑ ይኸን ያህ ጊዜ እነዲ ቆይ በነፃ የደከሙትን የቦርድ አባላትንና የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴን ማመስገን ተገቢ ነው፡፡
ይህን ሁሉ ሕዝብ ለማሰባሰብ፡ መስዋዕት የተከፈለው በገንዘብና የጉልበት ሥራ ብቻ ሳይሆን በሺዎቹ የሚቀጠሩ ልጆቻችንና ወንድሞቻችን ለአንድ ሳምት ውድደር ከስድስት ወር እስከ አንድ ዓመት ያላነሰ በየ አካቢያቸው ዝግጅት በማድረግ እንዲሁም ወደ ዘግጅቱ ለመምጣት ለጉዞአቸው ለስንቃቸው ገንዘብ በየመስራቤታቸው ትርፍ ሰዓት በመሥራት ገንዘብ አጠራቅመው፤በውድድሩም ጊዜም የጠዋት ብርድ የቀትር አሩር ፀሐይና ዝናብ ተፈራርቆባቸዋል፤በጨዋታው ላይም ብዙዎች በግጭት፡ ሲቆስሉ፤ ጭንቅላታቸው፡ እየ ተፈነ ከቱ፤ ትከሻቸው፤ ጉልበታቸው ክንዳቸውላይውልቃት የሚደረሰባቸውጥቂትአየደሉም፤በተለይምከሥራ ፈቃድ ሳየ ገ ኙ ውድድሩ አድምቀው ሲመለሱ ከሥራ የ ሚባረሩ ብዙዎች ናቸው፡፡እነዚህ ወጣቶች ለ30 ዓመት በመፈራረቅ ከፈተኝ መስዋዕት በመክፈላቸው ከፍያለ ምሰጋና አድናቆት ለቸራቸውይገባል፡፡
ማነኛውዝግጅት የሚያምረውና የዕድሜባለፃጋ የሚሆነውከሕዝብ ድጋፍ ሲያገኝ ብቻ ነው ለ30 ዓመታት በየስቴቱ ባደርግነው ዝግጅት ሁሉ ማለውሕብረተሰብ ድጋፍ በመስጠቱ ምስጋነችን ከፍያለ ነው፡፡
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ስፖርት ፈደሬሽን በሰሜን አሜሪካ ይኽን ያህል እድሜ ሲያስቆጥር ሁሉ ነገር ተመቻችቶለት እና መንገዶች ሁሉ አልጋ በአልጋ ሆነውለት ሳይሆን ከጥንሱ ጀምሮ የውስጥም ሆነ ከውጪየሚመጣበትን ችግር ሁሉ ሊቋቋም የቻለው የመነጋገርና የመቻቻል ልምድ ያዳበረ በመሆኑ ነው፡፡ ፌደሬሽናችን መቼም ቢሆን የ ግለሰቦችን ፍላጎ ት ከብዙኃኑ ፍላጎ ት አብልጦ ያስተናገደበት ጊዜ የለም ወደፊትም አየኖርም !! ዲሞክራሲያዊ ሂደቶችንም አይጥስም አይቀለብስም ስለዚህም ነ ው ጥቂት ግለሰቦች ፌደሬሽኑን በሚፈልጉት መንገድ ለመምራት ሲሞክሩ ትክክል ያለመሆናቸውን አስረድቶ የውይይት መድረክ ቢከፍትላቸው አንቀበልም ብለው ሌላ ፈደሬሽን አቋቁመው የ ፈደሬሽናችንን ስም እስከነ ምሕፃረ ቃሉ ሲጠቀሙየባለቤትነት መብታችን በመጠቀም በፍርድ ቤት ትእዛዝ ብናሳግድም ለሀያ ሥምንት ዓመታት የተጠቀምንበትን የጁላይ 4 ሣምንት (July 4 weekend) በመጠቀም ሕብረተሰቡን ለመከፋፈልና ፌደሬሽናችንን ለማዳከም ከኢትዮጵያዊነት ባሕል የወጣ ሥርዐት ለመከተል እየሞከሩ የ ሚገ ኙ ት ፡ ፡ የ ዚ ህ እ ኩ ይ ተ ግ ባ ር ውጤት ሕ ብ ረ ተ ሰ ባ ች ን ን መከ ፋ ፈ ል ብ ቻ ሳይሆን በሌሎች ሀገሮች የተከበርንበትንና የተደነቅንበትን ለብዙዎች አርአያ የሆንበትን ተግባር እያጠፉት ስለሆነ አጥብቀን እንቃወመው እናውግዘው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የዐፄ ካሌብ ወይም የቅዱስ ኤልስባን* ገድል - ፈንታሁን ጥሩነህ

ለ ሚቀ ጥ ሉ ት 2 0 ዓ መታ ት ኢ ት ዮ ጵ ያ ውያ ን በ የ አ መቱ በ አ ን ድ መድ ረ ክ ላ ይ እየተገናኘን የፌደሬሽናችንን የወርቅ ኢዮ በልዩ 50ኛ ዓመት እንድናከብር ምኞታችን ነው፡፡

ከብርሃኑ ወ/ማርያም

የኢትዮጵያ ስፖርትና ባሕል ፈደሬሽን በሰሜን አሜሪካ መስራች: የቀዲሞ ፕሬዘዳንት ባሁኑጊዜ የክብር ፕሬዘዳንት

(ESFNA founder,former president,current honorary president)

የ ኢትዮጵያ፡ ስፖርትና፡ የ ባሕል፡ ፈደሬሽን፡ በሰሜን፡ አሜረካ

(ESFNA) ለዘልዓለም ይኑር፡ ፡

Share