ዛሬ የአጼ ምኒልክ ልደት ነው

ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታቸው ከሸዋው ንጉስ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሤና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም ቅዳሜ ነሐሴ 12ቀን 1836ዓ.ም ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደዉ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ::

አያታቸዉ ንጉስ ሣህለ ሥላሴ የልጁን መወለድ ሲሰሙ “ምን ይልህ ሸዋ” በሉት ብለዉ ስም አወጡ::

እሳቸዉ “…… ምኒልክ በሚል ስም የሚነግስ ንጉሥ ኢትዮጵያን ታላቅ ያደርጋታል” የሚል ትንቢት ስለ ነበር ‘ምኒልክ’ የኔ ስም ነው ብለዉ ነበር::
ሆኖም በህልማቸዉ ከልጁ አብረው ቆመዉ ከሳቸዉ ጥላ የልጁ ጥላ በልጦ በእግር የረገጡትን መሬት ሲያለካኩ እሳቸዉ ከረገጡት ልጁ የረገጠዉ ረዝሞ አዩ::
ከዚህ በኃላ “ምኒልክ የኔ ስም አይደለም የሱ ነው ስሙን ምኒልክ በሉት” ብለዉ አዘዙ::
ጳዉሎስ ኞኞ
ከአጤ ምኒልክ መፅሐፍ

ተጨማሪ ያንብቡ:  Somali Refugees Fill UN Camp in Ethiopia Within One Month

3 Comments

    • HAPPY…..HAPPY….BIRTHDAY THE GREAT KING MENELIK…..The father of modern Ethiopia, the founder of Addis Ababa, the technology pioneer, the warrior and a well polished diplomat!!!!
      KING MENELIK the the pride of all black nations, the symbol of FREEDOM!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

Comments are closed.

Share