Hiber Radio : የተሳካውን የዋሽንግተን የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ስብሰባ አስመልክቶ ቃለ መጠይቅ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር፣ በአገር ቤት ሕዝቡ ከኤርትራ ለሚንቀሳቀሱ የነጻነት ታጋዮች ድጋፍ እንዳለው መገለጹ፣የመኢአድ የውጭ ግንኙነት ሀላፊ በማዕከላዊ በደረሰባቸው ድብደባ አካል ጉዳተኛ ሆኑ፣በሻንጣ ተደብቆ ስዊድን የገባው ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ትጘኝነት ጠየቀ፣የአገሪቱን የደህነት ባለሙያዎች አስገረመ፣ የደቡብ ሱዳን ተደራዳሪዎች የኢትዮጵያው አገዛዝን ሽምግልና ከራሱ ተቃዋሚዎች ጋር ያለተደራደረ ሲሉ አጣጣሉት ፣ሶማሌዎች ሰሞኑን በአገዛዙ ጦር ለተገደሉ ወገኖቻችን የደም ካሳ ይከፈለን ሲሉ መንግስታቸውን ጠየቁ እና ሌሎችም

/

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
የህብር ሬዲዮ ነሐሴ 10 ቀን 2007 ፕሮግራም

<…የዋሽንግተን ዲሲው ስብሰባ ሕዝቡ በቅርብ ዓመታት ከታየው የተለየ አንዳንዶች እንደሚሉት የቅንጅት ዘመንን የሚያስታውስ ነበር። የአቶ አንዳርጋቸው ፎቶ በጨረታ ከ70 ሺህ ዶላር በላይ የተሸጠበት ነው…ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በግንባር ከሰራዊቱ ጋር ሲያደርጉት የነበረው ውይይትና የሰጡት ምላሽ የሚያሳይ ፊልም ቀርቧል። ሕዝቡ ለሚደረገው እንቅስቃሴ ትልቅ ድጋፉን አሳይቷል…> ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሄደውን ደማቅ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ስብሰባ አስመልክቶ ከህብር ሬዲዮ ተጠይቆ ከሰጠው ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<…እዚህ አገር ቤት ሕዝቡ መንግስት የነጻነት ታጋዮችን እውቅና ላለመስጠት የኤርትራ መንግስት ትንኮሳ ፣የሻዕቢአ ተላላኪዎች የሚለውን ፕረፖጋንዳ አልተቀበለውም። ለነጻነት ትግሉ ድጋፍ ዓለው ወታቱ መቼ ነው የምንቀላቀለው ይላል ተማሯል …ያለንበት ሁኔታ ያው ድርቅ ቢባል ይሻላል ውሃ የለም፣መብራት የለም …> አንድ የደሴ ከተማ ነዋሪ በወቅታዊ ጉዳይ አነጋግረናቸው ከሰጡን ምላሽ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<…በውጭ ያለውን ኢትዮጵያዊ ለመደለል ይሄ ስርዓት ሲሞክር ይሄ የመጀመሪያው አይደለም። ዓላማቸው ለመከፋፈልና ለማዳከም በአገር ቤት በወገኑ ላይ የሚደረገውን ግፍ እንዳይቃወም ይህንን ለሚታገሉ እንዳይደግፍ ነበር ግን አይሳካም…ዲያስፖራ ያልማ የሚሉት ከዚህ የሚላከውን፣ከዕርዳታና ከብድር የሚወስዱትን እየዘረፉ መልሰው እያወጡ በምዕራቡ ዓለም የሚያከማቹትን ገንዘብ መጀመሪያ እነሱ ለምን አገር ቤት አያለሙበትም? ሰብኣዊ መብት የማይከበርበት፣የሕይወትና የንብረት ዋስትና በሌለበት አገር መቅደም ያለበት ነጻነት ማግኘቱ ነው…> ዶ/ር ሙሉጌታ ካሳሁን የቀድሞ የኢትዮጵያ ራዕይ ማህበር ሊቀመንበር ስርዓቱን ዲያስፖራን ለመከፋፈል ስለያዘው ያልተሳካ እቅድ ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…ሁበር ማለት የሰዎችን ሕይወት ለማናጋት የመጣ በአገር ቤት በአንድ ወቅት እንደሚባለው የአየር ባየር ንግድ አይነት ዩፎዎች ናቸው የማይጨበጡ…ሁበርና ሊፍት የአንድ ሳንቲም መንታ ገጽታ ናቸው። እዚህ እኛ ሁላችንም ተባብረን በጋራ ድምጻችንን አሰምተን ባለስልጣናቱ ሰምተውናል። ከኤርፖርት እንዳይጭኑ ተከልክለው እኛም በሁለት ሳንባችን መተንፈስ ጀምረናል…> አቶ ቁምላቸው መኩሪያ ሁበርን የሚቃወሙ ኢትዮጵያን አሽከርካሪዎች በሳን ሆሴ ስለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለህብር ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

በኢትዮጵያ ላይ ተጋረጠው የረሀብ እና ድርቅ አደጋ አስከፊነት በዓለም አቀፍ እና ከአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን እይታ (ልዩ ጥንቅር)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

በአገር ቤት ሕዝቡ ከኤርትራ ለሚንቀሳቀሱ የነጻነት ታጋዮች ድጋፍ እንዳለውና የአገዛዙን ፕሮፖጋንዳ አለመቀበሉ ተገለጸ

የመኢአድ የውጭ ግንኙነት በማዕከላዊ በደረሰባቸው ድብደባ የአካል ጉዳት ደረሰባቸው

ከኢትዮጵያ ወደ ስዊድን የሚሰደዱት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ጨመረ

በኢትዮጵያ አየር መንገድ በዕቃ መጫኛ አውሮፕላን ተሸሽጌ የገባው የፖለቲካ ጥገኝነት ጠየቀ

አዲስ አበባ ለድርድር የተቀመጡት የደቡብ ሱዳን ልዑካኖች የሕወሃት-ኢሕአዴግ አገዛዝን ዘለፉ

ከራሱ ተቃዋሚዎች ጋር ሳይደራደር ልሸምግል ማለቱን አጣጣሉት

ሶማሌዎች ሰሞኑን በኢህአዴግ ጦር ለተገደሉ ወገኖቻቸው የደም ካሳ ይከፈለን ሲሉ መንግስታቸውን ጠየቁ

ሁበርና ሊፍት በቬጋስ ስራ ለመጀመር በይፋ ማመልከቻቸውን አስገቡ

ሁበር ሰባት ሺህ ተሽከርካሪዎች ስራ ለማስጀመር እቅድ አለው

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ተጨማሪ ያንብቡ:  አቶ አንዳርጋቸው በየመን መንግስት ከታገቱ በሁዋላ የኢትዮጵያ ትምባሆ ድርጅት ለየመን ኩባንያ ተሰጠ
Share