August 12, 2015
3 mins read

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች በእያንዳንዳቸው የ15 ሺህ ብር ዋስ ተጠየቀባቸው

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ከምርጫው ማግስት ከአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በፖሊስ ተይዘው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች እያንዳንዳቸው 15 ሺህ ብር ዋስ ተጠየቀባቸው፡፡ አመራሮቹ ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ አራት ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፖሊስ በሽብርተኝነት ወንጀል እንደጠረጠራቸው ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ ፖሊስ ‹‹ለግንቦት 7 አባላትን እየመለመሉ ይልካሉ፡፡ ኤርትራ ድረስ ሄደው ስልጠና ወስደዋል፡፡›› የሚል ክስ አቅርቦባቸው የነበር ቢሆንም ለክሱ ምንም አይነት ማስረጃ ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ አመራሮቹ በበኩላቸው የታሰሩት በሰላማዊ ትግል ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ በመሆናቸው፣ በተለይም በምርጫው ወቅት ፓርቲያቸውን በማስተዋወቅና ህዝብን በማደራጀት ጠንካራ ስራ በመስራታቸው ገዥው ፓርቲ የወሰደባቸው በቀል መሆኑን ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡ ከመታሰራቸው በፊት የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ከፖለቲካው እንዲርቁ ሲያስጠነቅቁዋቸው እንደቆዩም አስታውቀዋል፡፡
ፖሊስ ላቀረበው ክስ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት ዛሬ ነሃሴ 6/2007 ዓ.ም ከምርጫው ማግስት እየታደኑ ከታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መካከል 8ቱ እያንዳንዳቸው የ15 ሺህ ብር ዋስ አቅርበው እንዲፈቱ ወስኗል፡፡ ከምርጫው በኋላ ታስረው በዛሬው ዕለት እያንዳንዳቸው 15 ሺህ ብር ዋስ ከፍለው እንዲወጡ የተጠየቀባቸው፡-
1. ልዑልሰገድ እምባቆም
2. ፋንታሁን ብዙአየሁ
3. መንግስቴ ታዴ
4. አበረ ሙሉ
5. አዳነ አለሙ
6. ሞላ የኑስ
7. ስማቸው ምንይችል
8. አበባው አያሌው ናቸው፡፡
ዛሬ ፍርድ ቤቱ በ15 ሺህ ብር ከፍለው ይውጡ ካላቸው በተጨማሪ በአማራና በደቡብ ክልል በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ታስረው እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተለይም ከተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎች ታድነው ከተያዙ በኋላ ባህርዳር ከተማ ውስጥ ታስረው የሚገኙት የፓርቲው አመራሮችና አባላት ከፍተኛ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Previous Story

ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት የመቶ ብር ኖቶችን እንደጉድ እያተማቸው ነው * መቶ ብር በዛ ኢኮኖሚ ጠነዛ

Next Story

በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በወረዳው አመራር ላይ በተወረወረው ቦምብ 2 ልጆች ሞቱ * አመራሩና ባለቤታቸው ቆስለዋል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop