በአማራ ክልል ሊመደብ የነበረው የኮማንዶ ጦር እቅድ ተሰረዘ * አለመተማመኑ በርትቷል

(ምንሊክ ሳልሳዊ) – የመጭው ምርጫ ጋር በተያያዘ ስጋቱ እያየለበት የመጣው የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አምባገነን ቡድን በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር እና በጎጃም ክፍለሃገራት ሊመድበው የነበረው የኮማንዶ ጦር እቅድ በጦሩ ውስጥ ያለውን ጉምጉምታ እና አለመተማመን ስላሳሰበው መሰረዙን እና ጦሩ ወደ ካምፕ እንዲመለስ መደረጉን ለጄኔራል ሰአረ መኮንን ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::
(ፎቶ ከፋይል)
ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በጦሩ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እና ሕዝቡ በጦሩ ላይ ጫና እንደፈጠረ እንዲሁም የከተማ ፖሊሶች የሕዝብ ወገንተኝነት ማሳየታቸው የፌዴራል ፖሊሶች ግምገማ የፈጠረው ችግር የደህንነቶች መክዳት የህዝቡ ለውጥ መሻት ተደማምሮ አለመተማመኖች በስርአቱ ውስጥ እየሰፋ እንዲሄድ አድርጎታል::በሰራዊቱ ውስጥ የተከሰተው አለመተማመን እየሰፋ እና እርስ በእርስ በጥርጣሬ መተያየት እየነገሰ መምጣቱ ሰራዊቱን በሕዝቡ መሃል ብናሰፍረው መሳሪያውን በመንግስት ባለስልጣናት ላይ ሊያዞር ስለሚችል በካምፕ እንዲቆይ እና በታትኖ ከአጋዚ ጦር ጋር መቀላቀል እና በተለያዩ አከባቢዎች ላይ እንዲመደብ የሚል ሃሳብ ቀርቧል::

የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ እየዳከረ በጠበንጃ ሃይል ሕዝብን ፈጅቶ ስልጣኑን ለማስረዘም እየሰራ መሆኑን ይታወቃል::ሰሞኑን የደረሱ መረጃዎች አዲስ አበባ በአጋዚ ጦር እና በፌዴራል ፖሊሶች እየተሸበረች መሆኗን መግለጹ ይታወሳል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  Ethiopia camp - 10 children a day die

2 Comments

  1. Please when you post news you make it full page on Facebook. So that any person in Ethiopia can see that. Otherwise useless because your pages is blocked in Ethiopia. ESAT corrected in such a way so Ethiopians can see its full news, but not yours.

  2. ye ethiopia behereseboch endih aynet yefetera propaganda eyenezu hager yemiyademu yesiltan timegnoch ena timkihtegnoch yemishekem jerba yelachewum. Timikihtegnoch ena weregnoch Be ethiopia beher bihereseboch kind yikesmalu.

Comments are closed.

Share