በኢብራሂም መሀመድ መዝገብ ተከሰው ከነበሩት 6 ቱ ላይ የቅጣት ወሳኔ ተላላፈባቸው

(ቢቢኤን. ሐሙስ ጥቅምት 27/2007) ስኔ 27 አሚሩ ድምፃችን ይሰማ ጠርቶት በነበረው ሰላማዊ ተቃውሞ በግፍ ተይዘው ታስረው ከነበሩት ወንድሞች መካከል 5ቱ ጥቅምት 24 በዋለው ችሎት ያቀረቡት የመከላኬያ ምስክር በቂ ነው በማለት በነፃ ተሰናብተው የነበረ ሲሆን በተቀሩት 6 ት ተከሳሾችን ደሞ ጥፋተኞች ናቸው በማለት ለቅጣት ውሳኔ ለዛሬ መቅጠሩ ይታወሳል።

ፍርድ ቤቱም ዛሬ በዋለው ችሎ ፍርደ ገምደልነቱን በግልፅ ያሳየ የፍርድ ቤቱን ካንጋሮነት ያረጋገጠ አሳፋሪ የቅጣት ወሳኔ መስጠቱን ለማወቅ ተችሎዋል።የቅጣት ውሳኔ ከተላለፈባቸው 6ቱ ንፁሀን ሙስሊሞች መካከል 10ኛ ተከሳሽ ሲቀር በሌሎቹ ላይ 1 አመት ከ 3 ወር የፈረድ ሲሆን 10ኛ ተከሳሽ ላይ ግን የ1 አመት ከ5 ወር የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፋን ለቢቢኤን ምንጮች ገልፀዋል።

በሌላ ዜና የህዝበ ሙስሊሙ መፍቴ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የመከላኬያ ምስክር በዛሬው እለትም ተደምጦ መዋሉን ታወቀ::

የሚሊዬን ኢትዬዺያውያን ሙስሊሞች ተወካይ የሆኑትና የሚሊዬን ኢትዬዺያውያንን ጥያቄ አንግበው በግፍ ለእስር የተዳረጉት የሳላም አንባሳደሮች የህዝበ ሙስሊሙ መፍቴ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ችሎት ዛሬ ቀጥሎ የዋለ ሲሆን መኪ መሀመድ በጭብጥ 11ና ሐይረዲን ከድር በጭብጥ 7 ለሰላም አንባሳደሮቹ የመከላኬያ ምስክር ሆነው ቀርበዋል።

የችሎቱ ቀዳሚ ምስክር የነበረው ወንድም መኪ መሀመድ በጭብጥ 11 የመሰከረ ሲሆን የመንግስት ታጣቂ ሀይሎች ወረሀ ሐምሌ 8 በአወሊያ ሊደርግ ታስቦ የነበረው የሰደቃና አንድነት ፕሮግራም ለማሰነዳት ሀምሌ 6 ምሽት ለፕሮግራሙ ዝግጅት ሲያደርጉ በነበሩት ንፁሀን ኢትዬዺያውያን ሙስሊሞች ላይ የወሰዱትን አስከፊ እርምጃና የፈፀሙትን መንግስታዊ ሽብር አስመልክቶ ለፍርድ ቤቱ ሰፍ ያለ ማብራሬያ ሰጥተዋል።መንግስት በእለቱ ሊደረግ የነበረው የሰደቃና አንድነት ፕሮግራም ለማደናቀፍ ሆን ብሎ በማሴር ያሰማራቸው የመንግስት ታጣቂ ሀይሎች የተከበረውን የምእመናን መስገጃና ፀሎት ማድረጌያ የሆነውን መስጂድ በመድፍር በንፁሀን ሙስሊሞች ላይ ከባድ የሆነ አካላዊም ስነ ልቦናዊም አደጋ ማድረሳቸውንም ጨምሮ ገልፆዋል በእለቱም በርካቶች የተደበደቡ እንደ ነበሩ በመግለፅ በተለይም በአሁኑ ሳአት ከህዝበ ሙስሊሙ መፍቴ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ጋ በግፍ በሀሰት ተከሰው በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞው የአወሊያ ተማሪና የካውንስል አባል ወንድም ሙባረክ አደምንና ሌላኛውን ወንድማችንን ሀለዲ ኢብራሂምን ከፍተኛ ድብደባ እንዳደረሱባቸውም ለፍርድ ቤቱ የዛሬው ምስክር የነበረው ወንድም መኪ መሀመድ ገልፆዋልዩ።በአጣቃላይ ሀምሌ 6 ምሽት አወሊያ ላይ የመንግስት ታጣቂ ሀይሎች ሲፈፅሙት የነበረው በደልና ግፍ ከገደብ ያለፈና እጅግ ሰባአዊነት የጎደለው ተግባር ሲፈፅሙ እንደ ነበረ ምስክሩ ጨምሮ ገልፆዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  "ዋርካውን በ3 ክፍለጦር ካልሆነ አንችለውም"

በእለቱ ችሎት ለሰላም አንባሳደሮቹ ሁለተኛ ምስክር ሆኖ የቀረበው ወንድም ሐይረዲን ከድር የነበረ ሲሆን በጭብጥ 7 ላይ መንግስት ሙስሊሙ መሀበረሰብ አንስቶዋቸው በነበሩት 3 ህጋዊና ህገ መንግስታዊ ጥያቄዎች ላይ ምን ያክል ጣልቃ ይገባ እንደነበረና በተለይም መስከረም 27 2004 ሊደረግ በነበረው ምርጫ ላይ መንግስት ሲያደርገው የነበረውን ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት አስመልክቶ ሰፋ ያለ ማብራሬያ ለድርድ ቤቱ ሰጥተዋል።በተለይም የመስከረም ወሩ ምርጫ ከመካሄዱ አስቀድሞ በተለያዩ የአዲስ አበባ ወረዳዎች ላይ ምርጫውን አስነልክቶ ስብሰባዎች ይካሄዱ እንደነበረ የገለፁት ምስክር በስብሰባዎቹ ላይ በሚሊዬን ኢትዬዺያውያን ሙስሊሞች የተመረጡትን የህዝበ ሙስሊሙን መፍቴ አፈለሰላጊ ኮሚቴዎችን ስም የማጥፋት ዘመቻ ማድረግና በተለይም ሙስሊሙ ማሀበረስብ ምርጫው እንዲካሄድ የጠየቀው መስጂድ መሆኑን ተከትሎ መንግስት የራሱን የግል አላማውን ለማሳካት በማሰብ ምርጫው መካሄድ ያለበት በቀበሌ ነው ሲል በተወካዬቹ በወረዳው ስራ አሰፈፃሚዎች በኩል ጫና ያሳድር እንደነበረም ምስክሩ ለፍርድ ቤቱ ጨምሮ ገልፀዋል። የእለቱ ችሎት በዚሁ የተጠናቀቀ ሲሆን የእለቱ ምስክር የነበሩት ወንድሞች ከሁለቱም የህግ ባለሞያዎች ለተነሱላቸው ዋናና መስቀለኛ ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ በመስጠት አሰገራሚ የመከላኬያ ምስክርነት ቃለቸውን ሰጥተዋል::

በእለቱ ከነዚ ሁለቱ ምስክሮቻ ጋ ለመመስከር ፍርድ ቤት ቀርበው የመበሩት ሁሴን ጣሂርና ሀይሪያ ሁሴን እነሱ ሊመሰክሩት የነበረው ጭብጥ ቀደም ሲል በመሰከሩት ምስክሮች ተገቢ በሆነ ሆኔታ በመብራራቱ የተከሳሽ ጠበቆች ገልፀው ቀሪዎቹ እንዲሰናበቱላቸው ጠይቀዋል በጠየቁትም መሰረት ሁለቱ ምስክሮቻችን በበቂ እንዲሰናበቱ ተደርጎዋል።
ህዝበ ሙስሊም ዛሬም እንደተለመድው ችሎት በመገኝት በመገኝት ለወካላቸው ንፁሀን መሪዎች ያለውን አጋርነት ገልፆዋል ችሎት በዚሁ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ የሰላም አንባሳደሮ የመከላኬያ ምስከር ለመስማል ለነገ ለአርብ ለጥቅምት 28/2007. ተቀጥሮዋል::
ነገም በሚኖረው ችሎት ህዝበ ሙስሊሙ የተለመደውን አጋርነቱን ይገልፃል ተብሎም ይጠበቃል

ተጨማሪ ያንብቡ:  ባህርዳር ከተማ ሁለት ዓይነት የተቃውሞ ሰልፎችን አስተናግዳለች
Share