ሕወሓት ሪከርድ በመስበር ቄሱን በሽብር ወንጀል ከሰሰች

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ እንደዘገበው፦

ቀሲስ ብርሃነ ቆባዕ (ከእግሪሓሪባ) በሽብር ተጠርጥረው (ከነ አደይ አልጋነሽ ጋ) ዛሬ ሰኞ ሰኔ 30, 2006 ዓም በፖሊስ ታሰሩ። ቀሲስ ብርሃነ እያረሱ እያሉ ነው በአራት ፖሊሶችና ስድስት ምልሻዎች ተከበው ከእርሻ ማሳ ታስረው ፖሊስ ጣብያ የገቡ። የነ ቀሺ ብርሃነ ጉዳይ ሽብር የሚል ነው። ህወሓት የኦርቶዶክስ ሀይማኖት አባት በሽብር በመክሰስ ሪከርድ ሰብራለች። ወይስ ቀስን በሽብር የከሰሰች ሌላ ሀገር አለች?
ጉድ ብዪ ሀገሬ ቄሱም፣ ሐጂውም፣ ኡስታዙም አሸባሪ ነው። እናቶችና የሀይማኖት አባቶች አሸባሪ ተሰኝተው የሚታሰሩበት ዘመን ደርሰናል። ካሁን በኋላ የእስልምና ሀይማኖት መሪዎች ብቻ አይደሉም በሽብርተኝነት የሚከሰሱ፤ የክርስትና ሀይማኖት አባቶችም አሸባሪዎች እየተባሉ ነው። በህወሓት ዘመን እስላም ክርስትያኑ አሸባሪ ተሰይሟል። አሁን ታድያ በሙስሊሞችና ክርስትያኖች መካከል መተባበር የሚያስፈልግ አይመስላችሁም? በቃ ሁላችን ሀይማኖት፣ ብሄር፣ ጎሳ ምናምን ሳንለይ አምባገነኑ የህወሓት ስርዓት ለመቀየር መተባበር አለብን። ሁላችን የስርዓቱ ሰለባ ነንና።
በሽብር የተከሰሱ የዓረና አባላት ቁጥር 8 ሲደርስ በተለያዩ ቦታዎች የታሰሩ የዓረና አባላት ቁጥር ደግሞ 115 ሆኗል። ቁጥሩ ለሳምንታት ታስረው የሚለቀቁና ደብዛቸው የጠፉ አይጨምርም።
ወይ ሽብር! በቃ ሁላችን አሸባሪዎች ነን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በጀርመን ሙኒክ ለአባይ ቦንድ ሽያጭ የተጠራው ስብሰባ በኢትዮጵያውያኑ ተቃውሞ አጋጠመው

5 Comments

  1. Brother Abreha I love what you write the way you think but do you think with ethnocentric parties like arena you can achieve real democracy in Ethiopia? Me I don’t think so. How do we achieve unity when we stand for our own ethnic only. Why don’t we stand for all people of Ethiopia as one .despite our many ethnic egos? No people shall discriminate against any ethnic and everybody is equal in the eye’s of justice.

  2. Abraha, I appreciate your uptodate information. But I haven’t heard anybody else not even your party denoucing and exposing such crimes

Comments are closed.

Share