June 27, 2014
1 min read

የተቃዋሚ አባላትን ማሰር ማወከብና ማፈናቀሉ ቀጥሏል

በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የሚኖሩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) አባሎች የሆኑት

– አቶ ሞላ ገረመው
– አቶ ብርሃኑ ገረመው
– አቶ ካሳሁን እንዳለ ከረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የተቃዋሚ አባል
በመሆናቸው ብቻ የሚያርሱትን መሬት ቀምተው አሳርሰውባቸዋል፡፡ ለምን እንቀማለን ዜጎች አይደለንም ወይ ብለው ተቃውሞ
ሲያሰሙ ከፓርቲው ለቃችሁ ካልወጣችሁ መሬታችሁ አይመለስም በማለት የቀበሌው ሊቀመንበር አቶ ፀጋዬ ጎሹ አስፈራርተዋቸዋል፡፡
እንዲሁም በምዕራብ ጎጃም በይልማና ዴንሳ ወረዳ (አዴት) የሚገኙ የመኢአድ አባላት ላይ እስርና አፈና የተፈጸመ ሲሆን አቶ በቃሉ
ደፋሩ የተባሉ የወረዳው አባል ከሳምንት በፊት በፖሊስ ተይዘው እስካሁን ፍ/ቤት አልቀረቡም፡፡
በዚሁ ወረዳ – አቶ አትገኝ እምሬ እንዲሁም
– ቄስ ይሁን ዘለቀ ከሐሙስ ሰኔ 19ቀን 2006ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት አይታወቅም ሲሉ የመኢአድ
የህ/ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አለምነህ ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

Source -https://www.facebook.com/MillionsOfVoicesForFreedomUdj?fref=nf

Previous Story

ESAT Radio Fri, June 27, 2014

Next Story

የአማራን ህዝብ በማጥፋት ወያኔና ተቃዋሚው በጋራ እየሰሩ ነው – ከወለጋ ከቄለም አካባቢ እና ከግንቢም ቁጥራቸው ከ2 ሺ እስከ 3 ሺ የሚደርስ የአማረኛ ተናጋሪዎች ተባረሩ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop