በእውቀቱ ስዩም ስለ ዞን 9 ጦማሪዎች፤ “የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም”

ታዋቂው የስነጽሁፍ ሰውና ኮሜዲያን በእውቀቱ ስዩም በፌስቡክ ገጹ በእስር ላይ ስለሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያን የሚከተለውን አስፍሯል።

ነጻነትና ፍትህ በሌሉበት አገር ውስጥ የልማት አውታሮችን መገንባት የት ለመድረስ ነው?የባቡር ሀዲድ ግንባታ ሳይ ፣የሚመጣብኝ እንደ አይሁድ በባቡር ታጭቀው ወደ መግደያ ጣቢያ የሚጓጓዙ ዜጎችን ነው፡፡የኤሌክትሪክ ግንባታ ሳይ የሚመጣብኝ የኤሌክትሪክ መግደያ ወንበር ነው፡፡የሚቆፈር ነገር ሳይ ድቅን የሚልብኝ የጅምላ መቃብር ነው፡፡

የዞን ዘጠኝ ጀግኖች ብረሳችሁ ታሪክ ይርሳኝ፡፡ባንድ በኩል የዘመናችሁ ተካፋይ በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡በሌላ በኩል፣ የመከራችሁ ተካፋይ ባለመሆኔ ሐፍረቱን አልችለውም፡፡ያም ሆኖ‹‹በሉ እናንተም ሂዱ እኛም ወደዛው ነው፡፡ወትሮም መንገደኛ ፊትና ኋላ ነው›› የሚለው የዓለሙ አጋ የበገና እንጉርጉሮ ባጸደ-ነፍስ ላሉት ብቻ ሳይሆን ባጸደ-ወህኒ ላሉትም ይሆናል፡፡ስሜቴን እንዴት መግለጽ እንዳለብኝ አላቅም፡፡የገላውድዮስ ዜና- መዋእል ጸሐፊ በዚህ ሰዓት የሚሰማኝ ስሜት ከምእተ አመታት በፊት ተሰምቶት ነበር፡፡
መዓልትኒ ኮነ ሌሊተ፣ዘኢነአምሮ ወጽልመት ዘኢልማድ መጽአ
ወደፈነ እንስሳ ወሰብአ
(ቀኑ ሌሊት ሆነና፣ ወጋገኑ ተሰደደ
እንግዳ ጨለማ መጣ፣ጠባዩ ያልተለመደ
ሰውን፣ እንስሳን ጋረደ)

ተጨማሪ ያንብቡ:  Hiber Radio: በሳዑዲ ትላንት ሁለት ኢትዮጵያውያን ተረጋግጠው ሞተዋል

6 Comments

  1. I really don’t know how I can put my anger in plain language about all the mess that EPRDF led by TPLF has done on my honorable country, ETHIOPIA.Do the so called understand what people and country mean? What have they done for us other than looting and killing? I wish I have contributed something crucial to skirmish this tyrannical, thorny, pugnacious government!

  2. I salute you Bewketu for the courage you have shown to speak up against the arrest and accusation of innocent journalists based on the usual and old fabricated lies by the mercenary regime land locked our country

    True development with out freedom is meaningless developing the country while dismantling the social fabrics holds together Ethiopians by inciting hatred and creating animosity between Ethinics is will lead to destruction of the infrustructures being built like as we have seen in It in AMBO
    As WOyane and OLFites continue with the current policy of creating animosity among Ethiopians no infrustructures will survive as our beloved country sinks to ethnic conflict like Somalia
    To sunup Woyane development is meaningless unless they change their mind and it has been proven they will not change their policy of destroying Ethiopia

  3. አባይ ሲገደብስ ምን ይሆን እፊቶ ድቅን የሚልብዎ? ልማት መቼ ይመቻችሁዋል ማማት እንጂ።

  4. Ewnetem Beweketu! Semen melak yawetawal malete ewnet yehonelete!

  5. Focus on your poetry where you are good at. Stop pleasing the twisted minds of the diaspora. You are right if you say” they won’t show up to my “show” if I do not unreasonably condemn this government.” Learn that there were 22 Gojames at the rank of ministers during the Dergue regime. Did they do anything valuable to this country? While in Ethiopia, you have been opening your mouth widely…it is naturally wide no doubt. If hatred to Tigrayans is freedom of speech, go hell. There won’t be any room for that.

Comments are closed.

Share