May 7, 2014
10 mins read

ትዴኢ አንድነትና መኢአድን ለመዋሐድ እየጣረ ነው ትዴኢ አንድነትና መኢአድን ለመዋሐድ እየጣረ ነው

በ  ዘሪሁን ሙሉጌታ /ሰንደቅ ጋዜጣጋዜጣ

የሰባት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው “ትብብር ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እንዲዋሐዱ የመጨረሻ ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

የትብብሩ ሰብሳቢ አቶ ግርማ በቀለ ትናንት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት “ትብብሩ” ሁለቱ ፓርቲዎች እንዲዋሐዱ ጥረት እያደረገ ያለው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በጉጉት ሲጠብቀው የቆየው ውህደት ያለበቂ ምክንያት የመስተጓጎል አዝማሚያ በማሳየቱ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ትብብሩ እንደባለድርሻ አካል ደግሞ በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለው ልዩነት በሰላም ተጠናቆ ውህደቱ እውን ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ የውህደት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ የራሱን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማድረግ ነው ብለዋል።

ትብብሩ ይሄንኑ ዓላማ ለማሳካት ከሁለቱም ፓርቲዎች ጋር ለመዋሐድ የውህደት ጥያቄ በደብዳቤ ማቅረቡን የገለፁት አቶ ግርማ የትብብሩ የመጀመሪያ ፍላጎት ሁለቱ ፓርቲዎች ውህደት ከተጠናቀቀ በኋላ ትብብሩ አዲስ ከሚፈጥረው ውህደት ጋር መልሶ መዋሐድ እንደሚፈልግ አስታውቀዋል።

ይሁን እንጂ በመኢአድና በአንድነት መካከል የሚደረገው ውህደት የማይሳካ ከሆነ ከሁለት አንዳቸው ጋር ለመዋሐድ መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት አቶ ግርማ ወደዚህ ውሳኔ ከመምጣታቸው በፊት ግን የሶስትዮሽ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርቲዎቹ ከመዋሐዳቸው በፊት የፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለምና የአደረጃጀት ጥያቄዎች በምን መልኩ ማስታረቅ እንዲሚቻል የተጠየቁት አቶ ግርማ፤ ችግሩ የርዕዮተዓለምና የአደረጃጀት አለመሆኑን ገልፀዋል። እሳቸው የሚመሩት “ትብብር” በአራት የክልልና በሶስት ህብረብሔራዊ ፓርቲዎች የተዋቀረ መሆኑን በማስታወስ ከመኢአድም ሆነ ከአንድነት ጋር ሊያዋህዳቸው የሚችለውን መሠረታዊ መነሻ አጥንተው ማጠናቀቃቸውን አስረድተዋል። ያስቸገራቸው ግን የተዋሐደ ፕሮግራም ያላቸው መኢአድና አንድነት ለመዋሐድ አለመወሰናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል።

“የአንድነትና የመኢአድ ፕሮግራም ስታየው ሁለቱ ያልተዋሐዱ ማን ሊዋሐድ ይችላል የሚል ጥያቄ ያጭርብሃል” የሚሉት አቶ ግርማ ትብብሩ እንደተፈለገው የሚሳካ ከሆነ በቅርቡ የሶስትዮሽ መግለጫ እንደሚሰጡ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ባለፈው ሰኞ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በዚሁ ጉዳይ ለመወያየት ኮረም ባለመሟላቱ ለመጪው ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ለማወቅ ተችሏል። በመኢአድ በኩል እስካሁን የውህደት በሩ አለመዘጋቱን ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ወገኖች እየገለፁ ነው። ሆኖም “ትዴኢ” ወደ አንድነት እንዲገባ በትብብሩ ላይ ግፊት እያደረገ ነው በሚል ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ የመኢአድ አመራሮች ስጋታቸውን ገልፀዋል።

“ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” ሰባት በብሔርና በህብረብሔር የተደራጁ በአመዛኙ በደቡብ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የተሰበሰቡትና በቅርቡም በይፋ መተባበራቸውን ያስታወቁ የፓርቲዎች ስብስብ መሆኑ አይዘነጋም።

የሰባት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው “ትብብር ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እንዲዋሐዱ የመጨረሻ ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ።

የትብብሩ ሰብሳቢ አቶ ግርማ በቀለ ትናንት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት “ትብብሩ” ሁለቱ ፓርቲዎች እንዲዋሐዱ ጥረት እያደረገ ያለው እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በጉጉት ሲጠብቀው የቆየው ውህደት ያለበቂ ምክንያት የመስተጓጎል አዝማሚያ በማሳየቱ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ትብብሩ እንደባለድርሻ አካል ደግሞ በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለው ልዩነት በሰላም ተጠናቆ ውህደቱ እውን ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ የውህደት ጥያቄ መልስ እንዲያገኝ የራሱን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማድረግ ነው ብለዋል።

ትብብሩ ይሄንኑ ዓላማ ለማሳካት ከሁለቱም ፓርቲዎች ጋር ለመዋሐድ የውህደት ጥያቄ በደብዳቤ ማቅረቡን የገለፁት አቶ ግርማ የትብብሩ የመጀመሪያ ፍላጎት ሁለቱ ፓርቲዎች ውህደት ከተጠናቀቀ በኋላ ትብብሩ አዲስ ከሚፈጥረው ውህደት ጋር መልሶ መዋሐድ እንደሚፈልግ አስታውቀዋል።

ይሁን እንጂ በመኢአድና በአንድነት መካከል የሚደረገው ውህደት የማይሳካ ከሆነ ከሁለት አንዳቸው ጋር ለመዋሐድ መዘጋጀታቸውን የጠቀሱት አቶ ግርማ ወደዚህ ውሳኔ ከመምጣታቸው በፊት ግን የሶስትዮሽ ውይይት እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

ፓርቲዎቹ ከመዋሐዳቸው በፊት የፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለምና የአደረጃጀት ጥያቄዎች በምን መልኩ ማስታረቅ እንዲሚቻል የተጠየቁት አቶ ግርማ፤ ችግሩ የርዕዮተዓለምና የአደረጃጀት አለመሆኑን ገልፀዋል። እሳቸው የሚመሩት “ትብብር” በአራት የክልልና በሶስት ህብረብሔራዊ ፓርቲዎች የተዋቀረ መሆኑን በማስታወስ ከመኢአድም ሆነ ከአንድነት ጋር ሊያዋህዳቸው የሚችለውን መሠረታዊ መነሻ አጥንተው ማጠናቀቃቸውን አስረድተዋል። ያስቸገራቸው ግን የተዋሐደ ፕሮግራም ያላቸው መኢአድና አንድነት ለመዋሐድ አለመወሰናቸው ነው ሲሉም ገልጸዋል።

“የአንድነትና የመኢአድ ፕሮግራም ስታየው ሁለቱ ያልተዋሐዱ ማን ሊዋሐድ ይችላል የሚል ጥያቄ ያጭርብሃል” የሚሉት አቶ ግርማ ትብብሩ እንደተፈለገው የሚሳካ ከሆነ በቅርቡ የሶስትዮሽ መግለጫ እንደሚሰጡ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

ባለፈው ሰኞ የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በዚሁ ጉዳይ ለመወያየት ኮረም ባለመሟላቱ ለመጪው ቅዳሜ ቀጠሮ መያዙ ለማወቅ ተችሏል። በመኢአድ በኩል እስካሁን የውህደት በሩ አለመዘጋቱን ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ወገኖች እየገለፁ ነው። ሆኖም “ትዴኢ” ወደ አንድነት እንዲገባ በትብብሩ ላይ ግፊት እያደረገ ነው በሚል ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ የመኢአድ አመራሮች ስጋታቸውን ገልፀዋል።

“ትብብር ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ” ወይም “ትብብር” ሰባት በብሔርና በህብረብሔር የተደራጁ በአመዛኙ በደቡብ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች የተሰበሰቡትና በቅርቡም በይፋ መተባበራቸውን ያስታወቁ የፓርቲዎች ስብስብ መሆኑ አይዘነጋም።

Weketawi2452
Previous Story

“የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ጥያቄ ፍትሐዊና ሕጋዊ ነው”

Wallaggaa2014 3
Next Story

ሰማያዊ ፓርቲ በተገደሉት ተማሪዎች ጉዳይ መግለጫ አወጣ፤ “የዜጎችን ጥያቄ በግድያ ማስቆም አይቻልም”

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop