April 4, 2014
2 mins read

አንድነት – ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን!! (ሰልፉ ለሚያዚያ 5 ተላለፈ )

UDJ Head

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY
(UDJ)
ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን!!
——————————————

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ በአዲስ አበባ ከተማ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ በመጣው የማህበራዊ ግልጋሎት አቅርቦት እጥረትናአለመመጣጠን ምክንያት መንግሥት በተደጋጋሚ ጊዜ የእርምት እርምጃዎችን እንዲወስድ ቢጠየቅም የወሰደው እርምጃ ባለመኖሩ ፓርቲያችን መጋቢት 28 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ‹‹የእሪታቀን›› በሚል መሪ ቃል ታላቅ ሠላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርግ ለህዝብ በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡

ሆኖም «የአዲስ አበባ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍልበመጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በቁጥር አ.አ ከስ/1ዐ/3ዐ.4/236 በላከልን ደብዳቤ ሠላማዊ ሠልፉን ለማድረግ በጠየቅንበት ቀን ተመሳሳይ የህዳሴ ግድብ ፕሮግራሞች ስላሉ ተለዋጭ ቀንእንድናቀርብ ጠይቆናል፡፡ በዚሁ መሠረት ለመጋቢት 28 ቀን 2ዐዐ6 ዓም ለማድረግ የያዝነውን ፕሮግራም ለማሸጋገር የህግ ግዴታ ስላለብን ለሚያዚያ 5 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ያዛወርን መሆኑንለኢትዮጵያ ሕዝብ በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት
መጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም
አዲስ አበባ

 

 

 

 

Previous Story

ጋዜጠኛ ሓገዞም መኮነን ተፈታ (አብርሃ ደስታ ከትግራይ)

Haile Medhin Abera
Next Story

ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ለማስመለስ የኢህአዴግ ልኡካን በጄኔቫ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop