May 3, 2023
5 mins read

ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ ከአል ቡርሃን ጋራ መሥራትን እንደሚመርጡ አስታወቁ

ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያይስ አፈወርቂ 1 1
#image_title

በሱዳን እየተፋለሙ ያሉ የጦር ጀነራሎች፣ በወኪሎቻቸው በኩል ለመደራደር ተስማምተዋል እየተባለ ውጊያው ግን በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት፤ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያይስ አፈወርቂ፣ መንግሥታቸው፥ ከሱዳን ጦር ጠቅላይ አዛዥ ጀነራል አብዱል ፈታሕ አልቡርሃን ጋራ መሥራትን እንደሚመርጥ አስታውቀዋል።

የቀድሞ የሱዳን ፕሬዚዳንት አልበሽር፣ እ.አ.አ. በ2019 በሕዝብ ተቃውሞ ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ፣ ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ፣ “ከሕዝብ ጋር የመወገን ሥራ ሠርቷል” ያሉትን በጀነራል አል ቡርሃን የሚመራውን ሠራዊት አድንቀዋል።

ላለፉት አራት ዓመታት፣ ኤርትራ ከሱዳን ጋራ አዎንታዊ በኾነ የሁለትዮሽ ግንኙነት መቆየትዋን ያወሱት ፕሬዚዳንቱ፣ ሱዳንን ለተፈላጊው ሽግግር የማብቃቱን ሓላፊነት መወጣት የሚችሉት፣ ጀነራል አል ቡርሃን እንደኾኑ ተስፋቸውን ገልጸዋል።

ሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች፣ በተደጋጋሚ ያደረጉት የተኩስ ማቆም ስምምነት ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሏል። በሁለቱ ጀነራሎች የሥልጣን ሽኩቻ ምክንያት የሚካሔደው ትጥቃዊ ፍልሚያ፣ በመቶዎች የሚቆጥሩ ሰዎችን ለኅልፈት ዳርጓል፤ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን፣ አገራቸውን ለቅቀው ለመሰደድ መጣደፋቸውን ቀጥለዋል።

ጎረቤት ሱዳን በዚኽ ጸጥታዊ ቀውስ ውስጥ በተዘፈቀችበት ኹኔታ፣ በትላንትናው ዕለት መግለጫ የሰጡት የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈ ወርቂ፣ ለሱዳን መታወክ ጥንስስ የኾነው ትልቁ ስሕተት የተፈጸመው፣ በፕሬዚዳንት ኣልበሽር አገዛዝ ወቅት ነበር ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል። “ሱዳናውያን እንደ አገር አንድ የመኾን ዕድላቸው አመዝኖ ሳለ፣ ደቡብ ሱዳን እንድትገነጠል መፍቀዳቸው፣ የአገሪቱ ቀንደኛ እና ታሪካዊ ስሕተት ነበር፤” ሲሉ አብራርተዋል።

ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ፣ በቃለ ምልልሱ ወቅት ያነሡት ሌላው ጉዳይ፣ ከሱዳን በመውጣት ላይ የሚገኙ ስደተኞችን አስመልክተው የተናገሩት ነው፡፡ ኤርትራ እንደ ጎረቤቶቿ ሀገራት ሁሉ፣ ስደተኞችን በመቀበል እና ወደ ሦስተኛ አገር በማሻገር የድርሻዋን ስትፈጽም መቆየትዋን ጠቅሰዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም፣ አሁንም ፖሊሲያችን፥ እንደ ዐቅማችን ተፈናቃዮችን ለመቀበል በራችንን ክፍት ማድረግ ነው፤ ብለዋል፡፡ ይኹንና፣ ተሰድደው ወደ ኤርትራ ለገቡ ችግረኞች መንግሥታቸው በሚከተለው መረዳጃ፣ “የሚዘረጋ የርዳታ ድንኳን የለም፤” ሲሉ፣ የስደተኞች ካምፕ የመክፈት ዕቅድ እንደሌላቸው አስታውቀዋል።

“አንድ እና የተዋሐደ ሠራዊት የመገንባት እና የሥልጣን ክፍፍል” የሚል አጀንዳ፣የሱዳን ግጭት ዋና ምክንያት እንደኾነ የሚጠቅሱት ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ፣ “እርባና የሌለው ምክንያት ነው” ሲሉ ተችተዋል፡፡ የጎረቤት አገሮች እና ሌሎች ኀይሎች ችግሩን ለመፍታት በሚል የሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት፣ አጋዥ ወይም ማሟያ እንጂ የኹነኛው መፍትሔ ተኪ ሊኾን እንደማይችል አሳስበዋል፡፡ ይልቁንም፣ እንደ ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አገላለጽ፣ የሱዳን ሕዝብ የራሱን ጉዳይ ራሱ ለመፍታት ዕድል እንዲሰጠው ጥሪ አቅርበዋል።

ሦስት ሳምንታት ያለፉት የሱዳኑ ትጥቃዊ ግጭት፣ ከ500 በላይ ሰዎች ለኅልፈት ሲዳረጉ፣ በ10ሺሕዎች የሚቆጠሩቱ ደግሞ መፈናቀላቸው እየተገለጸ ይገኛል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop