March 23, 2023
3 mins read

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የእያንዳንዳቸው “ውሳኔ” እንዲታወቅ – ሽፈራው

abiy and his parlama

በአሜሪካ የሕዝብ መብቶች (Civil Rights) ትግል ወቅት በአሜሪካ የኮንግረስ አባላት መካከል በ1960ዎች ከፍተኛ ትግል ተካሂዷል፡፡ ሲቪል ራይትስ ቢል በተደጋጋሚ ለውሳኔ ቢቀርብም ተቀባይነት አላገኘም ነበር፡፡ እጅ በማውጣት ብቻ ይወስኑ ነበር፡፡ ከውጭ ከፍተኛ የሕዝብ ግፊት ነገር ግን ዘረኛ ነጭ የምክር ቤት አባላት የጥቁር ሰዎችን መብት፣ ፀረ አድልዎ ሕጎችን በዘፈቀደ እጅ በማውጣት ያንቀበልም ውሳኔ ይወስኑ ነበር፡፡ በመጨረሻ እያንዳንቸው የምክር አባላት በእያንዳንዱ አንቀጽ ላይ ምን እንደወሰኑ በጽሁፍ እንዲቀመጥ ተወሰነ፡፡ ሕጉ ጸደቀ፡፡ የሕዝብ ጥላት ማን ነው? የሕዝብ መብት እንዳይፀድቅ የሕዝብ መብቶች እንዲነፈጉ የሚያደርጉ አባላት እነማን ናቸው? መታወቅ አለባቸው፡፡

ወያኔን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰኑ የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እንደዚያ ያለ አሰራር ቢኖር ያን ውሳኔ ይወስኑ ነበር?

ያ ቢሆን ለእኛም ይቀለን ነበር፡፡ ማንን ከኃላፊነት እና ከተወካይነት እንደምናነሳ እናውቅ ነበር፡፡ ወደፊት ማን በውሳኔው ተጠያቂ መሆን እንዳለበት እናውቅ ነበር፡፡ ማንም ለውሳኔው ኃላፊነት መውሰድ አለበት፡፡ ማንም ሊቀልድ አይገባም፡፡

ሰዎች እኮ ወያኔ ከሽብርተኝነት ይሰረዝ ያሉት ቁጥራቸው ስንት እንደሆነ እንኳ አልነገሩንም፡፡ ይህ ቀልድ ማብቃት አለበት፡፡ በሀገር እና በሕዝብ ላይ መቀለድ ማብቃት አለበት፡፡ እነርሱ ባይነግሩንም ማን ምን እንደወሰነ ማወቃችን አይቀርም፡፡ እናም እያንዳንዱ ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ሶስት ዓመት አለኝ የሚለው ዋስትና ከሆነው እናያለን፡፡

ይህ ውሳኔ ዳግም ለምክር ቤቱ መቅረብ አለበት፡፡ እያንዳንዱ አባል ምን እንደወሰነ በጽሁፍ መቀመጥ አለበት፡፡ በምክር ቤቱ ጉባዔ ያልተገኘ ሰው እንኳ ካለ በስልክ ተጠይቆ ውሳኔው መቀመጥ አለበት፡፡ ይህም ለሕዝብ ይፋ መደረግ አለበት፡፡ ውሳኔው እንደገና መታየት አለበት፡፡ ጉዳዩ እንደገና ለምክር ቤቱ መቅረብ አለበት፡፡ ግልፀኝነት ይጎድለዋል፡፡ ኃላፊነት ይጎድለዋል፡፡

ወያኔ ከሽብርተኝነት ዝርዝር መሰረዝ የለበትም

ጉዳዩ እንደገና መታየት አለበት፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

Go toTop