“አማርኛን የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ብሎም የዓለም ቋንቋ ልናደርገው ይገባል” ኒጀራዊት ጋዜጠኛ ራህመቶ ኪታ

አማርኛ ቋንቋን የኢትጵያውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ብሎም የዓለም ቋንቋ ማድረግ እንደሚገባ ኒጀራዊቷ ራህመቶ ኪታ ገለጸች፡፡

ጋዜጠኛ፣ የፊልም ዳይሬክተር፣ ፕሮዲዩሰር እንዲሁም የፍራንኮ አፍሪካን ፊልም አዋርድ አሸናፊ የሆነችው ራህመቶ ኪታ አማርኛን የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ ለማድረግ ከዓመታት በፊት እንቅስቃሴ መጀመሯን ተናግራ አሁን ላይም አማርኛን ይፋዊ የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ ተደርጎ ሊካተት እንደሚገባ እየሞገተች እንደሆነ ገልጻለች፡፡

እኛ አፍሪካውያን የራሳችንን ባህል በራሳችን ቋንቋ ካላስተዋወቅን የሌሎች ባህል ይወርሰናል የምትለው ራህመቶ አማርኛ የኢትዮጵውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን እንዲሁም የዓለም ቋንቋ ልናደርገው ይገባል ትላለች፡፡

ራህመቶ በአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባኤ ላይ የፓንአፍሪካ ፊልም ውይይትን ለመታደም ከሰሞኑ አዲስ አበባ የገባች ሲሆን አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በየዓመቱ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ቢሆንም ስለሚካሄደው ጉባዔ ከጥቂት ከተማሩ ኢትዮጵያውያን ውጪ ስለምን እንደሚወራ አይሰሙም፤ ይህም ሊሆን አይገባም ትላለች፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን አነጋግራ እንደነበር የገለጸችው ራህመቶ፤ በቅርቡም ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳፋኪ መሀመት ይፋዊ ደብዳቤ መስጠቷንና የኬንያውን ፕሬዚዳንት ማናገሯን ገልጻለች፡፡

በዓለም ላይ በርካታ ቋንቋዎች ቢኖሩም እንደ አማርኛ ጥንታዊ የሆኑ ቋንቋዎች ጥቂት በመሆናቸው መንከባከብና ማስተዋወቅ ይገባል ብላለች፡፡

ለዚህም ቋንቋውን በተሰማራችበት የፊልም ሙያ ለዓለም እያስተዋወቀች ትገኛለች፡፡

ቋንቋውን በኪነ ጥበቡ ከማስተዋወቅ አኳያ በቅርቡ በሰራችው ‹ዘ ዌዲንግ ሪንግ› የተሰኘ ፊልሟ ‹የጋብቻው ቀለበት› የሚል የአማርኛ ስያሜን በመስጠት በተጨማሪም በፊልሙ ላይ የተሳተፉ ተዋናዮችን ስም በአማርኛ በመጻፍ ቋንቋውን ለማስተዋወቅ ትልቅ ሚና አበርክታለች፡፡

ራህመቶ በአማርኛ ለመጻፍ የመረጠችበት ምክንያትም አማርኛ እጅግ ጥንታዊ ቋንቋ ከሆኑ የዓለማችን የጽሁፍ ቋንቋዎች አንዱ በመሆኑ እንደሆነ ተናግራለች፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጊዜ የወጣለት ፌደራል 5 ህጻናትን አንበርክኮ ፎቶ ይነሳባቸዋል (ፎቶ)

በዚህ ስራዋ ላይም ኢትዮጵያዊ የፊልም ባለሙያ የሆኑት ሀይሌ ገሪማ፣ ሰለሞን በቀለ እንዲሁም በኒጀር የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ክቡር አምባሳደር አማዱ ሀሰን ሜዳዋ ከፍተኛ ትብብር ማድረጋቸውን ገልጻ ምስጋናዋን አቅርባለች፡፡

በተጨማሪም በቀጣይነት ፊልሞቿን ወደ አማርኛ አስተርጉማ በኢትዮጵያ ለእይታ የማብቃት ፍላጎት እንዳላት ገልጻለች፡፡ ራህመቶ አማርኛ ቋንቋ የአፍሪካ ህብረት 7ኛ የህብረቱ ይፋዊ የስራ ቋንቋ እስኪሆን ጥረቴን አላቆምም ብላለች፡፡

ኢ ፕ ድ)

2 Comments

  1. የአማርኛ ቋንቋ
    አሁናዊ ከፍታና
    ምጥቀት ደረጃ
    ።።።።።።።።።።
    1ኛ/
    አማርኛ በUS አሜሪካ የመንግስት ቋንቋም ነው። እንዲያውም በአሜሪካዋ ቨርጂኒያ ግዛት አሌክሳንድሪያ ዳሽ የሚባለው የከተማ አውቶቢስ ላይ “እንኳን ወደ #WESTEND በደህና መጣችሁ!” የሚል ጽሁፍ ማየትም የተለመደ ነው።

    2ኛ/
    ለአፍሪካ ህብረትም ለስራ ቋንቋነት ቀርቧል። ቀድሞም የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እ.ኤ.አ በ1963 ሲመሰረት ቻርተሩ አፍሪካ በቀል በሆነው አፍሪካዊ ቋንቋ
    አፍሪካን በብቻው በመወከል በአማርኛ
    ተጽፎ ፀድቋል።

    3ኛ/
    በእስራኤልም ለስራ ቋንቋነት
    ታጭቷል።

    4ኛ/
    በጃማይካም ለመንግስት ዘርፍ ቀርቧል

    5ኛ/
    በቲሪንዳድና ቶቤጎ ከ75 በላይ እድባራት እየተገለገሉበት ነው

    6ኛ/
    Dstv’ም የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና፣የኦሊምፒክ ውድድሮችን ጨምሮ የእንግሊዝ ኘሪሚየር ሊግ ፣ የስፔን ላሊጋ ፣ የጣሊያን ሴ ሪ ኤ እንዲሁም ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎችን በአማርኛ ቋንቋ እንዲተላለፉ ከወሰነ አመት አስቆጥሯል።

    7ኛ/
    የአሜሪካ ሳይንቲስቶች 90% ይማሩታል።

    8ኛ/
    በሆሊውድ የፊልም እንዱስትሪ ውስጥ ገብቶ በካሚንግ አሜሪካ2 ፊልም ላይ ፊደላችን፣ አልባሳታችንና መስቀላችን ሳይቀር በፊልሙ ውስጥ ተከስቷል፣

    9ኛ/
    በሙዚቃውም በኩል ቢሆን እድሜ ለአቤል ተስፋዬ (aka the weeknd) አማርኛችንን ሆሊውድ መንደር እንዲደመጥ አድርጎታል!

    10ኛ/
    ራመቱ ኬይታ የተባለች ኒጄር /አፍሪካዊ ኮከብ አለም አቀፍ ፊልም መግለጫ ሆኖ አለም ላይ ይታይል።

    11ኛ/
    በአላም ላይ
    ከ15 ታላላቅ ዮኒበርሲቲዎች በላይ አንደ አንድ ትምህርት ይሰጣል።

    12ኛ/
    በአሜሪካ የሚገኙ ሳይንቲስቶች አብዛኛዎቹ ይማሩታል።

    አማርኛ፦

    13ኛ/
    በ2007 ዓ.ም.የአፕል የቴክኖሎጂ ማዕከል አማርኛን ከዓለም ግዙፍ ቋንቋዎች ተርታ መድቦ የቴክኖሎጂ ቋንቋ አድርጎታል።

    14ኛ/
    በ2008 ዓ.ም. የጎግል የቴክኖሎጂ ማዕከል የመተርጎሚያ ቋንቋ አድርጎታል።

    15ኛ/
    በኢትዮጵያ በስነ-ጽሑፍ ቅርስነት በዮኔስኮ ከተመዘገቡት መካከል፦

    – ታሪከ ነገስት ዘዳግማዊ ምኒልክ፣

    -ዐፄቴዎድሮስ ለእንግሊዝ ንግስት ቪክቶሪያ የፃፉት ደብዳቤ፣

    -ዳግማዊ ምኒልክ ለመስኮብ ቄሳር ዳግማዊ ኒኮላስ የፃፉት ደብዳቤና ሌሎችም በአማርኛ የተጻፋ ናቸው።

    16ኛ/
    አማርኛ ቋንቋ በአፍሪካ ምድር በስነ ጽሑፍ ሀብት የበለጸገ ብቸኛው እና ነባር ቋንቋ ሲሆን አማርኛ ቋንቋ በአንድ ድምፅ የኮምፒውተር መተግበሪያ ተሰርቶለት እንግሊዝኛ ቋንቋ በቀላሉ መጻፍም ተችሏል።

    በጉንደት፣በጉራዕ፣በአድዋ እና በማይጨው በተደረጉ ጦርነቶች ወታደሩን ከየብሄሩ ያሰባሰበ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቋንቋ ነው።

    መይሳው ካሳ (ዐፄ ቴዎድሮስ) ለእንግሊዝ ማስጠንቀቂያ የሰጠው በአማርኛ ነው።

    ዐፄ ዮሐንስ አዋጅ ያስነገረው በአማርኛ ነው።

    ዐፄ ምኒልክ አለምን ያስደነቀ አመራር የሰጠው በአማርኛ ነው።

    ዐፄ ኃይለሥላሴ ጀኔቫ ላይ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ንግግር ያደረጉት በአማርኛ ነው።

    መንግስቱ ኃይለማሪያም 17 አመታት ሀገሪቱን አንቀጥቅጦ የገዛው በአማርኛ ነው።

    መለስ ዜናዊ እድሜ ልኩንም አገር የመራው በአማርኛ ነው

  2. ውድ ወገኖች ሁሉ !
    1/ዶክተር አበራ ሞላ
    2/ ፓን አፍሪካኒስት
    ሞዴል የሀረር ወርቅ ጋሻው
    3/ አፍሪካ አሜሪካዊ ፓንአፍሪካኒስት ሚስተር ማርክ ፖውል
    4/ራመቱ ኪያታ ኒጄራዊት ፊልም አክተር
    5/ሲምባ ጃማ /ዚምባቢያዊ/
    6/ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ
    7/ ፕሮፌሰር
    ፍቅሬ ቶሎሳ
    1/ የኢትዮጽያን ብሄራዊ የስራ ቋንቋን አማርኛ የአፍሪካ ህብረት የስራ መገልገያ ቋንቋ እንዲሆን።
    2/ ኢትዮጵያ በቀል በአፍሪካ ብቸኛ የሆነውን አፍሪካዊ የኢትዮጽያ ፊደል የሁሉም አፍሪካዊ ቋንቋዎችና አገሮች መገልገያ እንዲሆን
    3/ ሰንደቅ አላማችን
    አረንጓዴ ብጫ ቀይ እብሪተኛውን ነጭ የቅኝ ገዥ በአፍሪካዊ ጥቁር ህዝብ ተሸንፎ አድዋ ላይ የትዋረደበት
    አብዛኛው 99% ፓንአፍሪካኒስቶችና
    የጥቁር ህዝብ ጀግንነት የቅኝ ገዥን ነጭን አሸንፎ መላሽነት ብሎም የነፃነት ተምሳሌትና ሰንደቅ አርአያነት ምልክት አድርጎ
    የኢትዮጵያ ባንዲራን የኣፍሪቃና የጥቁር ዘር ሁሉ ነፃነት፣ ኩራትና ክብር ነው በማለት መልኩን ከተከተሉት አብላጫ 95% ግድም የአፍሪካ አገሮች 10 አገራት አረንጓዴ ብጫ ቀይ ፍጹም አንድ አይነት
    ሌሎች 37 አገራት አንድ ወይም ሁለት መልክ የተደባለቀ ጠቅላላ ከ54ቱ 47ቱ የሚከተሉት አረንጓዴ ብጫ ቀይ ሰንደቅ አላማን ነው ስለዚህ የፓን የአፍሪካ
    ሰንደቅ አላማ እንዲሆን ለአገራችን ጥቅም ክብር መልካም ስም ከፍታና ዝና በትጋት እየሰሩ ናቸው።
    እኛም በትጋት በመጻፍ ኮሜንት በማረግና ሼር በማድረግ የየችሎታችንን እንድናግዛቸው ይገባናል.

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share