February 24, 2023
4 mins read

“አማርኛን የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ብሎም የዓለም ቋንቋ ልናደርገው ይገባል” ኒጀራዊት ጋዜጠኛ ራህመቶ ኪታ

333023024 1173428390205133 4163968906709598134 n 1 2አማርኛ ቋንቋን የኢትጵያውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን ብሎም የዓለም ቋንቋ ማድረግ እንደሚገባ ኒጀራዊቷ ራህመቶ ኪታ ገለጸች፡፡

ጋዜጠኛ፣ የፊልም ዳይሬክተር፣ ፕሮዲዩሰር እንዲሁም የፍራንኮ አፍሪካን ፊልም አዋርድ አሸናፊ የሆነችው ራህመቶ ኪታ አማርኛን የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ ለማድረግ ከዓመታት በፊት እንቅስቃሴ መጀመሯን ተናግራ አሁን ላይም አማርኛን ይፋዊ የአፍሪካ ህብረት የስራ ቋንቋ ተደርጎ ሊካተት እንደሚገባ እየሞገተች እንደሆነ ገልጻለች፡፡

እኛ አፍሪካውያን የራሳችንን ባህል በራሳችን ቋንቋ ካላስተዋወቅን የሌሎች ባህል ይወርሰናል የምትለው ራህመቶ አማርኛ የኢትዮጵውያን ብቻ ሳይሆን የአፍሪካውያን እንዲሁም የዓለም ቋንቋ ልናደርገው ይገባል ትላለች፡፡

ራህመቶ በአፍሪካ ህብረት መሪዎች ጉባኤ ላይ የፓንአፍሪካ ፊልም ውይይትን ለመታደም ከሰሞኑ አዲስ አበባ የገባች ሲሆን አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በየዓመቱ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ቢሆንም ስለሚካሄደው ጉባዔ ከጥቂት ከተማሩ ኢትዮጵያውያን ውጪ ስለምን እንደሚወራ አይሰሙም፤ ይህም ሊሆን አይገባም ትላለች፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን አነጋግራ እንደነበር የገለጸችው ራህመቶ፤ በቅርቡም ለአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳፋኪ መሀመት ይፋዊ ደብዳቤ መስጠቷንና የኬንያውን ፕሬዚዳንት ማናገሯን ገልጻለች፡፡

በዓለም ላይ በርካታ ቋንቋዎች ቢኖሩም እንደ አማርኛ ጥንታዊ የሆኑ ቋንቋዎች ጥቂት በመሆናቸው መንከባከብና ማስተዋወቅ ይገባል ብላለች፡፡

ለዚህም ቋንቋውን በተሰማራችበት የፊልም ሙያ ለዓለም እያስተዋወቀች ትገኛለች፡፡

ቋንቋውን በኪነ ጥበቡ ከማስተዋወቅ አኳያ በቅርቡ በሰራችው ‹ዘ ዌዲንግ ሪንግ› የተሰኘ ፊልሟ ‹የጋብቻው ቀለበት› የሚል የአማርኛ ስያሜን በመስጠት በተጨማሪም በፊልሙ ላይ የተሳተፉ ተዋናዮችን ስም በአማርኛ በመጻፍ ቋንቋውን ለማስተዋወቅ ትልቅ ሚና አበርክታለች፡፡

ራህመቶ በአማርኛ ለመጻፍ የመረጠችበት ምክንያትም አማርኛ እጅግ ጥንታዊ ቋንቋ ከሆኑ የዓለማችን የጽሁፍ ቋንቋዎች አንዱ በመሆኑ እንደሆነ ተናግራለች፡፡

በዚህ ስራዋ ላይም ኢትዮጵያዊ የፊልም ባለሙያ የሆኑት ሀይሌ ገሪማ፣ ሰለሞን በቀለ እንዲሁም በኒጀር የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ክቡር አምባሳደር አማዱ ሀሰን ሜዳዋ ከፍተኛ ትብብር ማድረጋቸውን ገልጻ ምስጋናዋን አቅርባለች፡፡

በተጨማሪም በቀጣይነት ፊልሞቿን ወደ አማርኛ አስተርጉማ በኢትዮጵያ ለእይታ የማብቃት ፍላጎት እንዳላት ገልጻለች፡፡ ራህመቶ አማርኛ ቋንቋ የአፍሪካ ህብረት 7ኛ የህብረቱ ይፋዊ የስራ ቋንቋ እስኪሆን ጥረቴን አላቆምም ብላለች፡፡

ኢ ፕ ድ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop