ድርድር እንጅ ይቅርታ አልጠየቅንም? ስምምነቱ ተጥሷል

ለማንኛውም የአብይ አህመድ “ሲኖዶሲ አባገዳ ይቅርታ ሳይሆን የነበረው ድርድር እንጅ ይቅርታ ልጠየቅንም: በጫካ የተሾሙት ቄሮዎች አልተሻሩም” ብሏል:: ኮንፊውዝ-ኮንቪንስ ስትራቴጂ ጅራቲ:)  ደራሲና አዘጋጅ አብይ አህመድ ሳይፈቅድ ይህ መግለጫ ስለማይሰጥ “ስምምነት” የተባለው ሰነድ ለባሰ ቀውስ የሚሆኑ የመርዝ ዘሮች ሆን ተብለው እንደገቡበት ስናስብ የባሰው ድራማ ከፊታችን ነው::  መቸስ በዚህ የሚገረም የዋህ እኮአሁንም አይጠፋም? በነገራችን ላይ አንድ ሰው ይቅርታ ጠየቀ የሚባለው ስህተቱን ሲምንና ፀፀትም ሲያሳይ ነው::   ያየነው ግን ከዚያ በተቃራኒ ነው::
ችግሩ “ኦሮሚያ” የምትባል እባጭ ሀገር በኢትዮጵያ ሞት ላይየማዋለድ ፅኑ የኦሮሙማ ፖለቲካ ስለሆነ መትሄ መሆን የነበረበትም ፖለቲካዊ ህዝባዊ ንቅናቄ ነው:: ነገር ግን ፖለቲካው በጃንደረባ ወዶ-ገቦችና ምንደኞች ከሽፏል:: ህዝቡም ዋጋ ከፍሎ ይህን የጃንረቦች ክህደት እስካልቀየረ ድረስ ኢትዮጵያም ጥንታዊቷ ቤ/ክንም ከባለፈው ሳምንት በበለጠ አደጋ ላይ ናቸው::
GK20230217

ተጨማሪ ያንብቡ:  "ትውልድና ሃገር እየገደሉ የተከበሩ መባል የለም!"

1 Comment

  1. የጠ/ሚኒስትሩ የቁማር ጨዋታ ግልጥ ነበር። በመጀመሪያ ቤተክርስትያኗ የጠራችው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይደረግ፤ ሰባብኮ ለስምምነት ተገናኙ ብሎ ማዘናጋት ነበር። ሰላማዊ ሰልፉ ቢደረግ ኖሮ፤ አንደኛ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት የሚሰለፉበት ነበር። ይህ ደግሞ ምን ያህል እንደሚያሰጋው ያውቃል፡፡ እናም ባለመደረጉ ዳነ። ቀጥሎ አስታራቂ ነኝ ብሎ አባቶችን ስለሃይማኖት መስበክ ጀመረ። ይሄ ደግሞ ጥሩ ሰው ትብሎ እንዲታይ መንገድ ከፈተለት። በመካከሉ እኔ ግን የለሁበትም! በማለት ራሱን ነፃ አውጣ። ነገሩ ግን ያው ተመልሶ ካለበት ተዘፈቀ። እናም አቸነፈ። ብጥብጡ እንደቀጠለ ነው። ቤተክርስትያን ግን ሊኖራት የሚችለውን ጉልበት ሳታሳይ ቀረች። አሁንም ሰላማዊ ሰልፉ ተጠርቶ መንግሥት ኃላፊነቱን እንዲወጣና በሃይማኖት ጣልቃ መግባቱን እንዲተው ካልተደረገ፤ ቤተክርስትያኗ ጤና አታገኝም።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share