February 17, 2023
10 mins read

ምልከታ (ክፍል-1) -ሸንቁጤ – ከካናዳ

331518137 3672090016351491 3181282135744743509 n 1በሃገሪቱ ላለፉት 30 አመታት ሲንተከተክ የቆየው ጠባብ ዘውጌኝነት  በተለይም ባለፉት 6 እና 7 አመታት ገንፍሎ በመውጣት  ያልነካካው እና ያላዳረሰው የህብረተሰብ እና ተቋማት ክፍል  የለም ::  በተለይም የህዝቦች  መተሳሰሪያ የሆኑት ማህበራዊ ድር እና እሴቶች( social fabrics and values) አንድ ባንድ ኢላማ ተደርገው እንዲበተኑ ሆኗል:: ቤተክርስቲያን የዚህ ማህበራዊ ድር ዋና ፈትል መሆኗ ደግሞ እንደ አሁኑ ገኖ እና ገዝፎ አይምጣ እንጂ ያለፈውን ሩብ ክፍለዘመን  የዘርፈ ብዙ  ጥቃቶች ኢላማ  እድትሆን አድርጏታል::

ላለፉት 2  ወይ  3 ሳምንታት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን ስታደርግ  የሰነበተችው

ትንቅንቅ  ህልውናዋን የተፈታተነ  ምዕመናንን ማቅ ያስለበሰ  ከ37 በላይ የሚሆኑትን በጥይት እና በደቦ የዱላ ቅጥቀጣ ህይወታቸውን የቀጠፈ  በሺዎች የሚቆጠሩትን  ወደ ጅምላ እስር  ያስጋዘ ቀሳውስቱን ይስደበደበ ያዋረደ እ ና ለእስር እና   እንግልት የዳረገ   ገና ያልተቋጨ  እና  ቀጣይ ፈተና እና ስቃይን የጋረጠ ክስተት ነበር::

 

ከላይ በግርድፉ  ሲታይ  ህዝብን  በአፍ መፍቻ “ቋንቋው ” ማገልገል   ሲጀመር ሃይማኖታዊ ግዴታ አለፍ ሲልም ከመብት መሰረታዊ ጥያቄነቱ  ባሻገር ለአንድ እምነት( ሃይማኖት) ቁልፍ የመስፋፊያ  ወይም ማዳረሻ መንገድ  መሆኑ ፈፅሞ  አሌ የሚባል አይደለም:: ላለፉት 30  አመታት ቤ/ክርስቲያኒቱ ከበቂ በላይ ሊባል ባይችል  እንኳ  የምትደርሳቸውን ምዕምናን ቋንቋ ና ባህል ያማከለ አገልግሎት ለማዳረስ አመርቂ ጥረት እና ውጤት የታየባቸው እንቅስቃሴዎች ማደረጏ የማይታበል ሃቅ ነው::

ይሁን እንጂ እነ አካለወልድ  አሁን ይዘውት የተነሱትን ጥያቄ  ሀቀኝነት  ለመበየን ተከታዮቹን አንኳር  ነጥቦች መመርመር  ለድምዳሜያችን አመክንዮ ጥሩ ግብዓት ይሆናል::

የነ አካለወልድ ጥያቄ እና አቋም   ሐይማኖታዊ እና ፍትሃዊ?

 

እነ አካለወልድ  ይዘው የተነሱትን አቋም ከግብ ለማድረስ የነማንን እርዳታ ሽተዋል ? አግኝተዋል? ከሰሞኑ የተከሰቱ ሁነቶችን ላየ እነዚህ ሰዎች ከጀርባቸው ያለው ፖለቲካዊ አጀንዳ ና ሃይል  ከውሃ ኩልል ብሎ ታይቷል:: ጥቂት ማሳያዎች :-

ስሞኑን ድምፁን ያጠፋው የኪሊማንጃሮው “የሰላም” ተጏዥ  ባንድወቅት ባካሄደው የባህር ማዶ ስብሰባ ” 3 ትም 4ትም ብትሆኑ እንኳን የራሳችሁን መስጂድ  የራሳችሁን ቤ/ክ  ክፈቱ(መስርቱ )  እያለ ሲደሰኩር ተደምጦ ነበር:: በዘውጌያዊው ንፍቀ ክበብ ካለው ተደማጭነት አንፃር ይህ  እንደ አቋም (policy) ተወስዷል  ብሎ መገመት ይቻላል::

በግምት የዛሬ 3 ዓመት ግድም  ተመሳሳይ ጥያቄ  በሲኖዶሱ ተነስቶ የነበረ ሲሆን ያኔም  ሽፋኑ “ቋንቋ”  ይሁን እንጂ  ግለሰቦቹ  በሚሰጡት መግለጫ እና ማብራሪያ ፍላጎታቸው የቤተክህነት ስልጣን እና የዘውግ መዋቅር  ያለው አደረጃጀት እንደሚሹ መሸሸግ አልቻሉም ነበር:: ይሄው ግብግብ  በወቅቱ የጠያቂዎቹ  አስተባባሪ ከሆኑት አንዱ   በሲኖዶሱ ከፍ ያለ ሹመት በማግኘታቸው ለጊዜውም ቢሆን ሊዳፈን ችሏል::

በሃገሪቱ  እየተቀረፁ  እና እየተተገበሩ ያሉ ፖሊሲዎች  እና እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች  የሚያሳዩት  ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር  እንደሃገር መቀጠሏ  ነገር  እጅግ አጠራጣሪ እየሆነ የታያቸው  ዘሬ ወደሚሉት በመንፏቀቅ  ይወክለኛል ለሚሉት ቡድን  አገር ምስረታ በውለታ መዝገብ መስፈርን እንደ  አንድ እድል(opportunity)  መጠቀምን መርጠዋል ::    እነ አካለወልድ ነፃይቱ ኦሮሚያ መመስረቷ እንደማይቀር  አምነዋል- እናም በነገይቱ ነፃ  ኦሮሚያ የታሪክ መዝገብ ” የኦሮሚያ ኦርቶዶክስ ሲኖዶስን የመሰረቱ” ተብለው መጠራት  ይህንኑ ተከትሎ የሚመጣው ዝና  ክብር  ስልጣን እና ምቾት  ስጋን የሚፈትን ነው::

የአካለወልድ  ቡድንን  የሚያደራጀው የሚደግፈውና  የሚዘውረው የመንግስት  እና  ሌሎች የፖለቲከኞች ቡድን  ካለፉት  አመታት ሁኔታ በግልፅ  የተረዱት  የሚፈልጉትን  ፖለቲካዊ  አጀንዳ የአንድ ዘውግ ስም እስከሰጡት ድረስ   ይህን አጀንዳቸውን እየደበደበ እየገደለ እና እየዘረፈ የሚያስፈፅምላቸው ስፍር ቁጥር  የሌለው ወጣት  እንዳለ  ነው:: ስለዚህ ያለምንም ሀፈረት እና  ይሉኝታ  የፈለጉትን  የማፍረስ  እና  የመበተን እርምጃ  በትእቢት እና ድንፋታ ጭምር በአደባባይ እየተሳደቡ እና እየፎከሩ በማስፈፀም ላይ ይገኛሉ:: ስራውን ይበልጥ ቀላል የሚያደርገው ደግሞ ” አማራ” እና ” አማርኛ” የሚሉትን ቃላት ጣል ማድረግ ነው –  በ ታሪካዊ በቀል ተተብትቦ  ያደገው ህልቆ መሳፍርት ወጣት  ሳያመነታ  በደቂቃዎች እንደሚነሳ  ከዚህ ቀደም በደቦ ፍርድ ( mob justice)  የተፈፀሙ ግድያዎች ስደቶች እና የንብረት ውድመቶች  ቋሚ ማሳያዎች ናቸው:: ለአሁኑ ክስተት ደግሞ ሻሸመኔ  እና የትዊተሩ “ኦርቶ- ማራ” ትርክት ዘመቻዎች አብነት ናቸው::

ሌላው  ከላይ ከተነሳው ነጥብ ጋር ተያያዥነት ያለው ክስተት እነአካለ ወልድን የሚዘውረው ቡድን የነዚህን ሰዎች ጥያቄ ዘውጋዊ መልክ እስካስዚያዘው ድረስ ምንም ጥያቄ እንደማይነሳበት እጅግ በመተማመኑ  ለ”ጵጵስና”  ያጫቸውን ግለሰቦች ግለታሪክ(profile) እንኳ  መለስ ብሎ ለማጥናት ባለመጨነቁ  ” በርጫም ጨብሲም  ሸሌም አለ” የሚሉ ዱርዬዎችን ጳጳስ አድርጎ መሾሙን ታዝበናል::

የጳጳሳት ሹመት ምዕመኑን በ”ቋንቋው” የማገልገል  ጥያቄን ይመልሳል? በየአጥቢያው እና አድባራቱ  ምዕመኑን  የሚገለግሉት  ካህናት ቀሳውስት እና ዲያቆናት ወይስ ጳጳሳት? አንድ  ጳጳስ  በስሩ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን በአመት ምን ያህል ግዜ ተገኝቶ  ያገለግላል?

እንደየአካባቢው ቋንቋ  ቀሳውስትን ዲያቆናትን እና መምህራንን የሚያሰለጥኑ መንፈሳዊ ኮሌጆች  መስፋፋት ወይስ የጵጵስና  ሹመት  እና የክልል ሲኖዶስ መመስረት ቀዳሚ አጀንዳ መሆን የነበረበት?

የመላውን የቤተክርስቲያኒቱ  አባላት ድጋፍ እና ይሁንታ ከመሻት ይልቅ የራሳቸው ዘውግ አባል የሆኑቱን ብቻ( ግንየእምነቱ ተከታይ ያልሆኑትን ጭምር ) ከጎናቸው ማሰለፉን ለምን መረጡ? ጵጵስና እና አባትነታቸው ለራሳቸው ብሄር አባላት ብቻ? ልንታደጋት ነው ከሚሏት ቤ/ ክ መሰረታዊ አስተምህሮ ጋር ይህ እርምጃቸው ይጣጣማል?

ተረማምደውበት የገቡት ደምና ሬሳ  በእረኝነት ሊያግዷቸው ( ሊጠብቋቸው) የሚገባ የክርስቲያን ነብሳት አይደሉምን? ለጠፉት ነብሳት ጥቂት እንኳን አዘኔታ ( empathy) ማሳየት ለምን ተሳናቸው?

 

( በክፍል 2  እመለሳለሁ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

Go toTop