January 4, 2023
5 mins read

ሕወሓትን ትጥቅ የማስፈታት ሒደት ሲጠናቀቅ የሽብርተኝነት ፍረጃው ተነስቶ ክስ እንደሚቋረጥ ተነገረ

322172698 685615496610497 6526858374599759364 n
ዮሐንስ አንበርብር

በደቡብ አፍሪካ በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሠረት የሕወሓት ታጣቂዎችን ሙሉ በሙሉ ትጥቅ የማስፈታት ሒደቱ ጫፍ ሲደርስ፣ በሕወሓት ላይ የተጣለው የሽብርኝነት ፍረጃ እንደሚነሳ፣ እንዲሁም በሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የተከፈተው የወንጀል ክስም እንደሚቋረጥ ተገለጸ።

ከሕወሓት ጋር የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ባለፈው ሳምንት ለተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ገለጻ ያደረጉት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮች አማካሪ ሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር)፣ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ለማዝለቅ በቀጣይ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ፣ በሕወሓት ላይ የተጣለውን የሽብርተኝነት ፍረጃ ማንሳትና ክስ ማቋረጥ እንደሚሆን ተናግረዋል።

ሬድዋን (አምባሳደር) ይህንኑ መረጃ ዓርብ ታኅሳስ 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከሕወሓት ጋር የተደረሰውን የሰላም ስምምነትና አፈጻጸሙን በተመለከተ ገለጻ ባደረጉበት ወቅት መናገራቸውን፣ የምክር ቤቱ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል።

ባለፈው ዓርብ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በተደረገው ገለጻ ላይ ከሬድዋን (አምባሳደር) በተጨማሪ፣ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎና የፍትሕ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ተገኝተው እንደነበር ምንጮች ጠቁመዋል።

317618662 5838013929598162 8861200791826146927 n

ሬድዋን (አምባሳደር) ለተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ገለጻ ባደረጉበት ወቅት፣ ‹‹የትጥቅ መፍታት ሒደቱ ጫፍ ሲደርስ ለፖለቲካ ሒደቱ በር መክፈት ስለሚያስፈልግ፣ ፓርላማው የሽብር ፍረጃውን ሊያነሳ ይችላል። የተመሠረተ የወንጀል ክስ ሒደትም እንዲቋረጥ የሚደረግበት ሁኔታ ይኖራል፤›› ብለው ነበር።

ይህ የሚደረገው ሰላም ለማምጣት ሲባል እንደሆነ የተናገሩት ሬድዋን (አምባሳደር)፣ ሽብርተኛ ተብሎ ከተፈረጀና የወንጀል ክስ ከተመሠረተበት አካል ጋር ቁጭ ብሎ መነጋገር ስለማይቻል፣ ክስ መቋረጥና የሽብርተኝነት ፍረጃው መነሳት እንዳለበት ገልጸዋል።

‹‹ሰላም ለማምጣት አንዳንድ መራራ አካሄዶች ይኖራሉ። ይህም ሰላምን ለማምጣት የሚከፈል ዋጋ ነው፤›› ብለዋል።

ወደ ፖለቲካ ውይይት ሲገባ ትኩረት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል ዋነኞቹ የሽግግር መንግሥት እንዴት ይቋቋማልና ምርጫ መቼ ይካሄዳል የሚሉት እንደሆኑም ገልጸዋል።

ሕወሓት በአሁኑ ወቅት ከባድ የጦር መሣሪያዎቹን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ያስረከበ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የመከላከያ ሠራዊቱ አንድ ሻለቃ ጦር ከባድ መሣሪያውን ተረክቦ በጥበቃ ላይ እንደሚገኝ የመከላከያ ሠራዊቱ አመራሮች ከሰሞኑ ለሚዲያዎች መግለጻቸው ይታወቃል።

ከዚህ በተጨማሪም የፌዴራል ፖሊስና የመከላከያ ሠራዊት አባላት ትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀሌን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ሰላም ለማስከበርና የፌዴራል ተቋማትን ለመጠበቅ መሰማራታቸውም ተገልጿል።

በአሁኑ ወቅትም የፌዴራል ፖሊስ ከመቀሌ ከተማ በተጨማሪ፣ በአዲግራትና በተከዜ አካባቢዎች፣ እንዲሁም ከማይጨው እስከ መቀሌ ባሉ ከተሞች እንደተሰማራ ታውቋል።

ሬድዋን (አምባሳደር) ለተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች ገለጻ ባደረጉበት ወቅት፣ የፀጥታን ማረጋገጥ ሥራ ከሕወሓት ጋር በጋራ የሚሠራ መሆኑን የጠቆሙ ሲሆን፣ ለዚህም ከሕወሓት በኩል ለፀጥታ ሥራ የተመረጡና የሠለጠኑ ኃይሎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ አስረድተው ነበር።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop