በንፋስ ስልክ ላፍቶ የመንግስት ታጣቂው የባለ3 ልጆች ባለትዳሮችን በጥይት ደብድቦ ገደለ

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)
ምኒልክ ሳልሳዊ እንደዘገበው

በንፋስ ስልክ ላፍቶ የመንግስት ታጣቂው የ3 ልጆችን ባልና ሚስትን በጥይት ደብድቦ መግደሉ ተሰማ። ድርጊቱ የተፈፀመው ትላንት ከቀኑ 9.30 አካባቢ ነው ተብሏል።

አዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ውስጥ ልዩ ስሙ መካኒሳ አቦ ማዞሪያ በሚባል አካባቢ አንድ የመንግስት ታጣቂ የሶስት ልጆች ወላጆች የሆኑትን ባልና ሚስት በአውቶማቲክ መቺንገን በጥይት ደብድቦ ገድሏቸዋል።

የአካባቢው ሰዎች እና የሟች ዘመዶች በጋራ በመሆን የቀብሩን ስነ- ሥርዓት ለማስፈጸምና የመንግስት ታጣቂው የወሰደው እርምጃ ለማውገዝ እና በየጊዘው በአካባቢው የሚፈጸመውን የመንግስት ታጣቂዎች እርምጃ እና በህብረተሰቡ ላይ የደረሰውን ግፍ በጋራ ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ለማጋለጥ በህብረት ድምጻቸውን ለማሰማት ሲሞክሩ በፈደራል ፖሊስ የተበተኑ ሲሆን በአካባቢው ላይ የአዲስ አበባ የፖሊስ ሃይሎች ተሰማርተዋል።

የፈደራል ፖሊስ አመራሮች የአከባቢውን ህዝብ የፖለቲካ አጀንዳ ያለው ሲሉት የፈረጁት ሲሆን ቀብሩ ሳይፈጸም ህዝቡን በማስፈራራት እና በዛቻ ያባረሩት ሲሆን የሟች ዘመዶች የኢትዮጵያ ህዝብ ይህን ጉዳችንን ሳይሰማና ሳያውቅልን አንቀብርም ብለው አስከረኖቹ ወደ መኖሪያ ቤት ተመስልሷል።

ለዘ-ሐበሻ ዘግየት ብሎ በደረሰን መረጃ ቀብሩ በነገው እለት ይፈጸማል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ወደ አዲስ አበባ እየመጡ የነበሩ 4 የሕዝብ ማመላለሻና አንድ የጭነት ተሸከርካሪዎች መታገታቸው ተሰምቷል

2 Comments

  1. This is typical TPLF strategy of eliminating those who do not conform to its twisted political view. Such brutal killings happen every day around our beloved country. Some are killed silently, others are killed in the open and the rest are poisoned or vanished in their underground prisons.
    What is not amazing is TPLF’s coverup of the killings. They do not want people to know, yet people know they are sick minded. Is this the freedom they boast about? Wiping an entire family for no reason? And partitioning and selling the land of our country? woe to those who call evil good.

Comments are closed.

Share