March 2, 2022
5 mins read

ንጉሱ አብይ በአድዋ የፈጸመው ገድል – ምስጋናው አንዷለም

275123329 10226856236822716 3131391021088315584 n
እነሆ ስም አጠራሯ በሻሻ በተባለች አንዲት አገር አንድ አይነ ገብ፣ መልከ መልካም እና ቁመተ ረዥም ልጅ ነበረ፡፡ ይህ ልጅም አባቱ ይሁኑ እናቱ አልታወቁም እንጅ በተወለደ ጊዜ ስሙን አብዮት አሉት፡፡ አስራ አራት አመት በሆነውም ጊዜ አቦይ ስብሀት ለተባሉ የትግሬ አገር ባላባት በአደራ ልጅነት ተሰጠ፡፡ የአቦይ ስብሀትን ምክር በመቀበልም አብዮት የተባለውን ስሙን ወደ አብይ ቀየረ፡፡ አቦይ ስብሀት አብዮት የሚለው ስም የደርጊ ጸላኢ ስም ነው ብለው ነበርና አብዮት በሚለው ስሙ ሊጠራ አልሆነለትም፡፡ ስሙን አብይ ብሎ በቀየረ ጊዜም እኒህ የትግሬ ባላባት ደስ አላቸው፤ ወደዱት፤ ማንጁስ አሉት፡፡ ሌሎቹም የትግሬ ሹማምንት ማንጁስ እያሉት ይላላክላቸው ነበር፡፡ የባላባቱ አቦይ ስብሀትም ስልክ ጠላፊ ሆነ፡፡
ብዙዎችንም የትግሬው ባላባት ጠላት የሆኑ አረመኔዎች አማራዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ሶማሌዎች፣ ጉራጌዎች እና የአዲስ አበባ ሰዎች ወደ እስርቤት ያስወረወር ነበር፡፡ አሳዳጊውን አቦይ ስብሀትን ለማስደሰት ከነበረው ፍላጎት የተነሳም ለአይኑ ደስ ያላሉትን ሁሉ ያስር እና ያስደበድብ ነበር፡፡
ከእለታት አንድ ቀንም የእናትና አባት ሀይማኖቱን ቀይሮ ክርስቲያን ሆነ፡፡ አሳዳጊው አቦይ ስብሀትም ደስ አላቸው፡፡ ምንም እንኳ አቦይ ስብሀት ኮሚኒስት የተባለውን ሀይማኖት ቢከተሉም ለክርስቲያኖች አልፎ አልፎ በጎ እይታ ነበራቸውና ይህ አብይ በፊታቸው ሞገስ አገኘ፡፡ ይህ አብይም ክርስቲያን ከሆነ በኋላ የጠለፈው ስልክ ቀድሞ ያደርግ ከነበረው የበለጠ ሆነ፡፡ የትግሬ አገር ስዎችም፤ ንጉሱን መለስ ዜናዊን ጨምሮ፤ ወደዱት፡፡ አረመኔዎችን አማራዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ሱማሌዎች፣ ጉራጌዎችና የአዲስ አበባ ሰዎችንም እንዲያጠፋላቸው ተስፋ አደረጉበት፡፡ ብዙዎችንም አጠፋላቸው፡፡ የትግሬ አገር ሰዎችም ከጠላቶቻቸው አርፈው ብዙ አመት ገዙ፣ ነዱ፣ ዘፈኑ፣ በሉ፣ ጠጡ፣ ደስም አላቸው፡፡ ይህ አብይ የተባለውም ስልክ ጠላፊ ወታደር እንዲሁ ያደርግ ነበር፡፡
ከእለታት አንድ ቀንም ጥልያን የተባለ ከባህር ማዶ የሆነ፤ እጅግም ከራቀ ምድር የሆነ፣ መንግስት ሀገረ ኢትዮጵያን አስገብሬ እገዛለሁ፤ ስሜንም እተክልባታለሁ ብሎ እልፍ ጦር አስከትሎ መጣ፡፡ ይህም አብይ የተባለው ስልክ ጠላፊ ወታደር በትግሬው ባላባት ይሁንታ የበሻሻ፣ ወንጭና ጨለንቆ ገዥ ሆኖ ተሾመ፡፡ በአምባላይ ፈረሱም ላይ ተቀምጦ አድዋ ወደተባለው አሚጸኛው ጥልያን በመሸገበት ተራራ ላይ ደረሰ፡፡ በፈረሱ ሽህ፣ በጎራዲውም ሽህ የጥልያን ሰራዊት ፈጀ፡፡ ጥልያንም በየካቲት ጊዮርጊስ እለት በዚህ ብርቱ ስልክ ጠላፊ ወታደር አብይ ሀይል ተደቆሰ፡፡
በየቦታው ተበታትኖ ውሀ ውሀ ይልም ነበር፡፡ ይህም አብይ ውሀ ውሀ ለሚሉት ጥልያኖች አንዳንድ ችግኝ ለጥላ ይሆና ቸው ዘንድ እጎናቸው ትከሉላቸው አለ፡፡ በዚህም አድራጎቱ የአድዋ ተራራ በዛፍ ተሸፈነ፡፡ ይህም ስልክ ጠላፊ አብይ የካቲት ጊዮርጊስ በሆነ እለት ሁሉ ይከበር ይዘከር ነበር፡፡
——————————-

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop