June 11, 2014
5 mins read

በሐረር የተገኘ የጅምላ መቃብር ጥያቄ አስነሳ

በሐረሪ ክልል ሐረር ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ሐማሬሳ ቀበሌ ውስጥ ሰሞኑን በተገኘ የጅምላ መቃብር ምክንያት አንዳንድ የከተማው ነዋሪዎች ጥያቄ ማንሳታቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

ሰሞኑን አካባቢው ለጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጆች ሼድ መሥሪያ ሲቆፈር በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች አፅም መገኘቱን የጠቆሙት ምንጮች፣ የከተማው አስተዳደር ቁፋሮ እንዲቆም ቢያዝም፣ አንዳንድ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ መቆፈር እንዳለበትና በጅምላ የተቀበሩት ዜጎች ቁጥር መታወቅ እንዳለበት በመግለጽ ተቃውሞ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡

ቦታው በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የሦስተኛው ክፍለ ጦር መቀመጫ እንደነበርና በደርግ ዘመነ መንግሥትም የጦር ካምፕ ሆኖ መቀጠሉ ታውቋል፡፡

ምንጮች እንደሚሉት በተለይ በደርግ ዘመነ መንግሥት በርካታ ወጣቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገድለው በጅምላ ተቀብረዋል፡፡ ኢሕአዴግ አገሪቱን እንደተቆጣጠረ በተለያዩ አካባቢዎች በጅምላ የተቀበሩ ዜጎች አስከሬንን ማስወጣቱ ይታወሳል፡፡ በሐረር ከተማም በዘመኑ በሰዎች ላይ ግድያ በጅምላና በተናጠል የተፈጸመ ቢሆንም፣ የተቀበሩበት ቦታ አለመታወቁና ጠቋሚ በመጥፋቱ እስካሁን ድረስ አስከሬኖች ሳይገኙ መቆየታቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያን ለ17 ዓመታት ሲመሩ የነበሩት ሌተና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያምም፣ አሁን የጅምላ መቃብሩ በተገኘበት ቦታ ላይ የነበረው የሦስተኛው ክፍለ ጦር አባል እንደነበሩ የገለጹት ምንጮች፣ ሥልጣን ከያዙ በኋላ ተቃውሞ ባደረጉ የኢትዮጵያ ወጣቶችና የወቅቱን ሥርዓት ተቃዋሚዎች ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ ሁሉንም የአገሪቱን ክልሎች ያዳረሰ ለመሆኑ፣ የሐረሩ የጅምላ መቃብር መገኘት ማጠናከሪያ ማስረጃ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሐረር በተገኘው የጅምላ መቃብር ምክንያት በወቅቱ ለተሰው ዜጎች ማስታወሻ እንዲሆን ሐውልት ሊቆም እንደሚገባ አንዳንድ ነዋሪዎች የከተማ አስተዳደሩን መጠየቃቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

በሐረሪ ክልል ሐረር ከተማ አካባቢ ተገኘ ስለተባለው የጅምላ መቃብርና አንዳንድ ነዋሪዎች አንስተዋል ስለተባለው ተቃውሞ ማብራሪያ እንዲሰጥ የክልሉ መስተዳደር ለመጠየቅ ቢሞከርም ምላሽ ማግኘት አልተቻለም፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንደገለጹት፣ የጅምላ መቃብር መገኘቱ እውነት ነው፡፡ የተገኘውም ቦታውን ለጥቃቅንና ለአነስተኛ ተደራጆች ሼድ ሠርቶ ለመስጠት ቁፋሮ ሲደረግ መሆኑን አረጋግጠው፣ አንዳንድ የግል አጀንዳቸውን ለማራመድ ሰበብ የሚፈልጉ ግለሰቦች ሕዝቡን ከለላ አድርገው ለመንቀሳቀስ ሞክረዋል ብለዋል፡፡ ሕዝቡ ሊተባበራቸው ባለመቻሉ አፍረው እንቅስቃሴያቸውን ማቆማቸውንም አስረድተዋል፡፡ ቁፋሮውም እንዲቆም ተደርጎ የክልሉ መንግሥት እየተነጋገረበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

Previous Story

በጋምቤላ ክልል ጎደሬ ልዩ ስሙ ዱንቻ አማርኛ ተናጋሪ ዜጎች ተፈናቀሉ ‪

addis ababa realethiopia 141
Next Story

በአዲስ አበባ የመሬት አስተዳደር ቢሮና በሌሎች ተቋማት ላይ ፓርላማ ዕርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop