December 2, 2014
5 mins read

በደቡብ ወሎ ዞን ኮምቦልቻ 5000 ሄክታር በሚጠጋ እርሻ ላይ ውድመት ደረሰ

(ፍኖተ ነፃነት) የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የኮምቦልቻ ከተማ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በ07 ቀበሌ ልዩ ስሙ ትዩ አምባ የሚኖሩ አርሶ አደሮች ላይ በቱርካውያን የባቡር መስመር ዝርጋታ ካምፓኒ የደረሰውን የአዝእርት ጭፍጨፋ በአካል በመሄድ የመስክ ግምገማና ምልከታ እንዲሁም ከአርሶ አደሮች ጋር ውይይት ማካሄዱን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ ፡፡

ለዝግጅት ክፍላችን በደረሰው መረጃ መሰረት ህዳር 21 ቀን 2007 ዓ.ም አምስት አባላትን ያካተተው በኮምቦልቻ የአንድነት ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በቦታው ድረስ በመሄድ የመስክ ጉብኝት ያደረገ ሲሆን በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የደረሰውን ጉዳት ገምግሟል፡፡ በዚህም መሰረት አምስት ሺህ ሄክታር በሚጠጋ የአርሶ አደሩ እርሻ ላይ ከፍተኛ የሆነ ውድመት መድረሱን ጉዳት የደረሰበት ማሳም በደረሱ የጤፍ፣ የስንዴ፤ የማሽላ እንዲሁም ሌሎች አዝእርቶች የተሸፈነ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ በስፍራው ተገኝተው የደረሰውን ጉዳት ያስረዱት ከ100 በላይ አርሶ አደሮች “ያለኛ ስምምነት፤ ተገቢው ካሳ ሳይከፈለን እንዲሁም አዝእርታችንን እንኳን ሳናነሳ ላባችንን ያፈሰስንበትን ምርት በግሬደር ከአፈር ጋር ደባልቀውታል” ብለዋል፡፡

አቶ መሀመድ ሰይድ የተባሉ አርሶ አደር እንደገለፁት የአዝእርት ማጥፋት ድርጊቱ ሲፈፀም በቦታው የነበርኩ ቢሆንም በህግ አምላክ ልፋታችንን ገደል አታስገቡብን፤ ምርታችንን እንኳ እናንሳ ብንልም ከቱርካውያኑ ጋር የተመደቡ ፖሊሶች በሙስና በታገዱት ከንቲባ የተፈረመ ደብዳቤ በማሳየት ታዘናል፤ ልማት ለማደናቀፍ ከሆነ እናስራችኋለን፤ ምንም አታመጡም እንደተባሉ በምሬት አስረድተዋል፡፡ የተሰበሰቡት አርሶ አደሮች “አርሰን እንኳ መብላት ካልቻልን ከንግዲህ ሀገርም የለን፤ ሀገራችንን ያሳዩን፤ ከተፈጥሮ ጋር ታግለን፤ ያለማነውን አዝመራ መንግስት ካጠፋው፤ ነገ የማዳበሪያ እዳ ክፈሉ መባላችን ስለማይቀር ያለን እጣ ፈንታ ሀገር ጥሎ መሰደድ ነው” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

በአካባቢው የሚገኝ ቀበሌ አስተዳዳሪ ለማነጋገር ባደረግነው ጥረት “እኛ ከበላይ ታዘን ነው፤ ፈፅሙ የተባልነውን ነው የፈፀምነው” በማለት መልሰዋል፡፡ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የቱርካውያኑን ካምፓኒ እና የከተማ አስተዳደሩን ኃላፊዎች ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ አርሶ አደሮቹ ወዴት አቤት እንደምንል ባለማወቃችን እየተፈፀመብን ያለውን ግፍና መከራ ቁጭ ብለን ለማየት ተገደን ቆይተናል አሁን ግን ህዝቡን በማስተባበር ከአንድነት ፓርቲ ጋር በመሆን ተቃውሟችንን እናሰማለን፤ የደረሰብንን መንግስታዊ ግፍ ለመላው ኢትዮጵያዊ አሰሙልን በማለት በስፍራው ለተገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች አሳስበዋል፡፡

በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ስር ካሉት የገጠር ቀበሌዎች (07 ቱሉ አዳሜ፤ 09 ትዩ አምባ፤ 010 መጠኔ እና 011 ጋሌሳ) የሚባሉ ቀበሌዎች ተካተው ይገኛሉ፡፡ እስካሁን ባገኘነው መረጃ መሰረት በእያንዳንዱ ቀበሌ በአማካይ 2000 (ሁለት ሺህ) አባወራ አርሶ አደሮች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ አራት የገጠር ቀበሌዎች በኢንቨስትመንት ሰበብ ከፍተኛ የሆነ የመሬት ቅርምት የሚካሄድባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop