ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ተሸለመ

እስክንድር ነጋ

ሰኔ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የ2014 “የጎልደን ፔን ኦፍ ፍሪደም” ሽልማት አሸናፊ የሆነው እስክንድርነጋ ዛሬ ሽልማቱን ተቀበለ።

በጣሊያን ቶሪኖ በተካሄደው የሽልማት ስነ-ስር ዓት ላይ እስክንድርን ወክሎ ሽልማቱን የተቀበለው በቃሊቲእስርላይየነበረው ስዊድናዊ ጋዜጠኛ ማርቲን ሽብዬ ነው።

“ምኞቴ ይህን ሽልማት እኔ እንድቀበለው አልነበረም” በማለት ንግግሩን የጀመረው ማርቲን፣ “ዛሬ ጠዋት ስነሳ ምናለ፦“ ተፈታሁኮ፤ ሽልማቱን እኔ ራሴ ልቀበል እመጣለሁ” የሚል ስልክ ከአዲስ አበባ በስልክ ብሰማ ብዬ ተመኝሁ” ብሎአል።

“ይህ ግን አልሆነም፤ ከሰ ዓታት በፊት እስክንድር ነጋ በዱላቸው የታሰሩባትን ክፍል ግድግዳ እየመቱ በማይክራፎን “ቆጠራ!ቆጠራ!” እያሉ በሚጮኹ የወህኒ ጠባቂዎች ድምጽ ነው ከመኝታው የተነሳው” ያለው ማርቲን፣ የሙያ ባልደረባውን ወክሎ ሽልማቱን ሊቀበል በስፍራው መገኘቱን ግልጾአል።

“ምንም እንኩዋን ከሲያ እስር ቤት ነጻ እንደሆንኩ ባስብም፤ ከትስታዎቹና ከእስር ቤቱ ድምጾች ፈጽሞ ነጻ ልሆን አልችልም”ሲልም ማርቲን ተናግሮአል።

ማርቲን በሲሁ ንግግሩ እስክንድር በእስር ቤት እየደረሰበት ያለውን ስቃይ እና የቃሊቲ እስር ቤትን አስከፊና አስቀያሚ ገጽታዎች በበቂ ሁኔታ ለታዳሚዎቹ አሳይቶአል።

እስክንድር ህግን ጥሰሀል ተብሎ ለእስር የተዳረገው መንግስትን በመተቸቱ እንደሆነ ያወሳው ማርቲን፤ “ይህ የሚያም ቀልድ ነው”ብሎ አል።

“ይህ የጎልደን ፔን ሽልማት፤ ከ1000 ቀናት በላይ በእስር ላሳለፈው ለእስክንድር ነጋ ብቻ ሳይሆን እስክንድርን ለእስር ለዳረገው ለጋዜጠኝነት ሙያ ጭምር የተሰጠ ክብር እንደሆነ ይሰማኛል” ሲልም ለሽልማቱ ያለውን አክብሮት ገልጾአል።

እስክንድር በአካል ከደረሰበት ቅጣት በላይ ከቤተሰቡ እና ከሚወደው ብቸኛ ልጁ በመለያዬት የደረሰባት የመንፈስ ቅጣት የከፋ እንደሆነም ማርቲን አመልክቱዋል።

እስክንድር የተማረ እና በሌላ ሙያ ሊሰማራ እየቻለ በጨቁዋኞች እጅ እየተሰቃየ የሚገኘው ለእውነት ባለው የጸና አቁዋም እና ለሀገሩ ባለው ፍቅር ምክንያት እንደሆነም ገልጾአል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የጨነቀው መከላከያ ከባህርዳር የተሠማው|ከዳባት የድል ዜና ፣ እንጅባራ ሰበር|ጎንደር የመንግስት ሃይሎች አሳዛ'ኝ ዜና

Source: Ethsat

Share