June 8, 2014
3 mins read

የስብሰባ ጥሪ- የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የጋራ ግብረሃይል የፊታችን ጁን 15, 2014 ህዝባዊ ውይይት አዘጋጅቷል

የስብሰባ ጥሪ

በአገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት 23 አመታት በተለያየ መልኩ በጋራ እንዳንቆም ሲያጋጨን የቆየው የወያኔ አገዛዝ የመጨረሻ ካርዱን በመሳብ የቋንቋ እና የሀይማኖት ልዩነቶቻችን ጌጣችን መሆናቸው ቀርቶ እርስ በርስ የምንጋጭባቸው አጀንዳዎች እንዲሆኑ ሌት ከቀን እየሰራ ይገኛል:: አገራችን ኢትዮጵያ አሁን የምትገኝበትን ተጨባጭ ሁኔታ ለተመለከተውና ለተገነዘበው ሁሉ፤ መጪው ጊዜ እንቅልፍ የሚነሳና የአገራችን ሰላምና ህልውና ፈተና ላይ መውደቁን ያስገነዝበናል።

ይሄንን ወያኔ የቀበረውን የጥፋት ፈንጂ በአገርና በወገን ፍቅር እንዲሁም በብልሀትና በዘዴ ካላመከነው በስተቀር፣ የአገራችን የወደፊት እጣ ፈንታ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱ አይቀሬ ነው:: ስለዚህ በውጭ የምንገኝ ወገኖች የመፍትሄው አካል ነንና ልናደርገው የምንችለውን ነገር ለማድረግ እንድንችል የመጀመሪያው መፍትሄ ግልጽ ውይይት ማድረግ ነው ብለን እናምናለን።

ስለዚህ ይህን በጎሳ እና በሀይማኖት ስም የተደገሰልንን የእልቂት ድግስ በዘዴ እንድንወጣው የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የጋራ ግብረሃይል የፊታችን ጁን 15, 2014 ህዝባዊ ውይይት አዘጋጅቷል።

በዚህ እና ተዛማጅ ወቅታዊ ችግሮቻችንን ላይ በግልፅና በጥልቀት ለመወያዬት የመፍትሄ ሃሳቦችን እንዲጠቁሙን የተለየዩ ምሁራንን እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦችን ለውይይት ጋብዘናል፤ እርሰዎም ከተጋባዦቹ ጋር በጋራ እንዲመክሩና እንዲሁም የሚሰማዎትን ጥያቄ እንዲያቀርቡ ተጋብዘዋል።
ተጋባዥ እንግዶች፥

ፕሮፈሰር ቲዮዶር ቨስታል
አቶ ኤፍሬም ማዴቦ
ዶክተር ኑሩ ደደፎ
ዶክተር አልማዝ ዘውዴ
ጋዜጠኛና አክቲቪስት አበበ ገላው

ቀን: እሁድ ጁን 15, 2014
ቦታ: 7701 16th Street, NW Washington, DC. 20012
ሰአት: 3PM
አዘጋጅ: የዋሽንግቶን ዲሲ የጋራ ግብረ ሀይል
ለበለጠ መረጃ: ስልክ (202) 556-3078 ኢሜል dcjointtaskforce@gmail.com

nazret3
Previous Story

የሚሊዮኖች ድምጽ – ለነገዉ የአዳማ ሰልፍ ቅስቀሳው ቀጥሏል – (ፎቶዎች ይመልከቱ)

deberemarcos 2
Next Story

የዛሬው የሚሊዮኖች ድምጽ በአዳማ እና ደብረ ማርቆስ የተቃውሞ ሰልፍ (LIVE UPDATE)

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop