ደብረማርቆስ አዳማ እና ቁጫ ሰኔ አንድ ቀን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች ይካሄዱባቸዋል።

አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መሪ ቃል ሁለተኛውን ዙር ህዝባዊ ንቅናቄ
በእለተ እሁድ ሰኔ አንድ ቀን 2006 በደብረማርቆስ በአዳማ እና በቁጫ ወረዳ በሰላማዊ ሰልፍ የህዝቡን የመሬት ባለቤትነት ጥያቄ ለማሰማት አደባባይ ይወጣል።
ሰላማዊ ሰልፎቹ እንደመጀመሪያው ዙር የሚሊዮኖች ድምጽ … የደመቁ እንድሚሆኑ ሲጠበቅ በከተማው የምትገኙ ነዋሪዎቹምበሰላማዊ ሰልፉ ላይ በመሳተፍ የታፈነ ድምጻችሁን እንድታሰሙ አንድነት ፓርቲ በአክብሮት ጋብዞታል።
ኑና ስለመሬታችን በጋር እንምከር ይላል የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት የሰልፉ አዘጋጅ ።

አንድነት ቅስቀሳውን አፋፍሞታል፤ ፖሊስ 19 አባላትን አስሯል


አንድነት ፓርቲ በመጪው ዕሁድ ሰኔ 1 ቀን 2006 በደብረማርቆስ፣ በአዳማ/ናዝሬት እና በቁጫ/ሰላም በር ከተማ የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት በሚል መሪ ቃል ለሚያካሂደው የተቃውሞ ሰልፍ፤ የቅስቀሳ ስራውን የሚያስተባብሩ ሶስት ቡድኖች ከትላንት ጀምሮ ከዋናው ጽ/ቤት መንቀሳቀስ ጀምረዋል፡፡ ዛሬ በቁጫ/ሰላም በር ከተማ የሚደረገውን ቅስቀሳ የሚያስተባብረው ቡድን ወደ ስፍራው አቅንቷል፡፡ በደብረ ማርቆስና በአዳማ የተጠናከረ ቅስቀሳ ከተሰራ በኋላ የፖሊስ የተሟላ የዕውቅና ማስረጃ የያዙት 10 የአንድነትን ደብረ ማርቆስ ላይ እንሁም 9 የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ደግሞ አዳማላይ አስሯል፤ በተጨማሪም የአንድነት ፓርቲ የአዳማ ከተማ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆነው አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላን ከሌሎች አመራሮችና አባላት ተነጥሎ እንደታሰረም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎UDJ‬‪#‎millionsofvoicesforlandownership‬ ‪#‎Adama‬ ‪#‎Debremarkos‬ ‪#‎Kucha‬

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዶ/ር ሰማኸኝ ጋሹና ሶሊያና ሽመልስ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ በሥልጣን ቅበላ ንግግራቸው ወቅት ያነሷቸው - SbS Amharic
Share