April 30, 2014
2 mins read

ከአዲስ አበባ ፕላን ተማሪዎቹ አይቀድሙም?

2 n
ዳዊት ሰሎሞን

በዛ ካሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየሰማናቸው የምንገኛቸው ዜናዎች አስደንጋጭ ናቸው፡፡ለነገሩ ገዢው ፓርቲ የሚከተለው ሩሲያን ከመፈረካከስ ያላደነ የፖለቲካ መስመር እንዲህ አይነት ፍሬ ማፍራቱ የማይጠበቅ አልነበረም፡፡እናም የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ተማሪዎች የአዲስ አበባ አካባቢዎችን ወደ አዲስ አበባ ይጠቀልላል የሚል ስጋት ባሳደረባቸው የከተማይቱ ማስተር ፕላን ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለጽ የተቃውሞ ሰልፎችን ለማድረግ ዝግጅት አጠናቅቀው ወደ ትገበራው ሲያመሩ ግጭት ተፈጥሮ በዛ ያሉ ተማሪዎች መጎዳታቸውን ሰምቼያለሁ፡፡


በእኔ እምነት ማስተር ፕላኑን ያዘጋጀ አካል ፊት ለፊት ቀርቦ ለመነጋገር ስህተት ከተሰራም እርማት ለመውሰድ ለምን እንደማይደፍር አይገባኝም፡፡መቼም ተማሪዎቹ ተቃውሞ ያቀረቡት መሬታችን ተቆርሶ ለባዕድ አገር ሊሰጥብን ነው በማለት አይመስለኝም፡፡ስጋታቸው ቤተሰቦቻቸው ከያዟት ኩርማን መሬት ጋር የሚጋመድ ይመስለኛል፡፡ ነገ ቤተሰቦቻቸቸው የያዟትን ኩርማን መሬት በሊዝ ለአንዱ ባለ ጊዜ ተሰጥታ ፎሪ እንዳይወጡ ሳይሰጉ አልቀሩም፡፡ይህንን ስጋት በፖሊስ ቆመጥና በፌደራል መሳሪያ ማስወገድ ይቻላል እስካልተባለ ድረስ መነጋገር መቅደም ይኖርበታል፡፡


እባካችሁ ለንግግር ዕድል ስጡ፡፡

Previous Story

ሰማያዊ ፓርቲ የአርበኞችን ቀን ሊያከብር ነው – በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቅጣት ተጣለባቸው

179
Next Story

በአንድነት ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ላይ ዘመቻ ተከፍቷል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop