የአዲስ አበባ አስተዳደር ሰማያዊ ፓርቲ እሁድ የጠራውን ሰልፍ እኛ በምንለው መሠረት ካላደረጋችሁ ፎርም አትሞሉም አለ (ደብዳቤውን ይዘናል)

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ ቤት በዛሬው ቀን ለሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ ፎርም መሙላት አለባችሁ በሚል ጥሪ አድርጎ የነበረ ቢሆን ወደ ቢሮው ካቀኑ በኋላ ‹‹ሰልፉን የምታደርጉት እኛ በምንለው መሰረት ካልሆነ ፎርሙን አትሞሉም›› እንዳላቸው ታውቋል፡፡ አመራሮቹም ደብዳቤ በጻፋችሁልን መሰረት ፎርሙን ካልሞላን ከቢሮ አንወጣም ብለዋል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ ቅስቀሳውና ሌሎች ለሰላማዊ ሰልፉ የሚደረጉት ዝግጅቶች አሁንም ቀጥለዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአማራ ሕዝብ ከሰልፍ ወደ ሰይፍ | መንግስት በፋኖ መሸነፉን አመነ| ክልሉን ፋኖ ቀማኝ | ባህር ዳር ተገባደደ |
Share