April 16, 2014
5 mins read

ሰማያዊ በፌደራል መንግስቱና በቡለን ወረዳ የመሰረተው ክስ ሀሙስ ፍርድ ቤት ይቀርባል!

ሰማያዊ ፓርቲ በቤንሻንጉል ጉምዝ በህገ ወጥ መንገድ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ቦታቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱና ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው በተደጋጋሚ ባካሄዳቸው ሰላማዊ ሰልፎችና ባወጣቸው መግለጫዎች የጠየቀ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው ምላሽ ባለመስጠቱ ዜጎቹ የተፈናቀሉበትን ቡለን ወረዳና የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ላይ ክስ መስርቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ክሱን ታዋቂው የዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ ዶክተር ያእቆብ ኃይለ ማሪያም ይዘውት የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ቢሮክራሲያዊ ምክንያቶች መዝገብ ሳይከፈትለት እንደቆየ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡
ይሁን እንጂ ሰማያዊ ፓርቲ ባደረገው ተደጋጋሚ ግፊት ክሱ በአሁኑ ወቅት መዝገብ ተከፍቶለት፣ የዳኝነት ክፍያ ተከፍሎ በቀጣይ ሀሙስ ሚያዝያ 9/2006ዓ/ም ክሱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሃብሄር ችሎት ላይ መታየት እንደሚጀምር ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በጉዳዩ ላይ አቋም ወስዶበት ከሰላማዊ ሰልፉም ባሻገር ዜጎቹ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱና ካሳ እንዲሰጣቸው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ እስካሁንም ድረስ በዜጎች ላይ በሚደርሰው ችግር ከጎናቸው ሆኖ የሞራልና የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡›› ያሉት አቶ ብርሃኑ ፓርቲው ኢትዮጵያውያኑ በመፈናቀሉ ሂደት በደረሰባቸው ችግር ልጆቻቸው የታመሙባቸውን ለህክምና እንዲሁም ለመጓጓዣም ፓርቲው እገዛ ሲያደርግ መቆየቱንና አሁንም ዜጎቹ ፍትህ እስኪያገኙ ድረስ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አሳውቀዋል፡፡
በፍርድ ቤት በተያዘ ጉዳይ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸው ትክክል ነው ወይ ብለን ላነሳንላቸው ጥያቄ ‹‹አሁንም ማፈናቀሉ ቀጥሏል፡፡ አሁንም ዜጎች እየተፈናቀሉ ስለመሆኑ በተለያዩ ሚዲያዎች ተዘግቧል፡፡ አሁንም ሰልፉን የጠራንበት ምክንያት ይህ የማፈናቀል ህገወጥ ድርጊት ባለመቆሙ ነው፡፡ እኛ እየከሰስን ያለነው ባለፈው የመፈናቀል ህገወጥ ተግባር በተፈጸመባቸው ላይ ነው፡፡ የቡለን ወረዳ ቀኑን ጠቅሶ ‹‹ስለምትፈናቀሉ ልቀቁ!›› ያለበትን ማስታወቂያና ማስጠንቀቂያዎች በመረጃነት ይዘናል፡፡ ይህ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ነው፡፡ ይህን ጥያቄ ማንሳት ደግሞ ዋነኛው ስራችን ነው፡፡›› ብለዋል፡፡
ኃላፊው አክለውም ‹‹አሁን ይህ ድርጊት ከወረዳና ከክልሎች አልፎ የመንግስት ፖሊሲ ወደመሆን በመሸጋገሩ በተደራጀና ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ መታገል አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡›› ብለዋል፡፡ የሰልፉ አላማም በኢህአዴግ የፖሊሲ ችግር ላይ መሆኑን የገለጹት የህዝብ ግንኙነቱ ‹‹ኢህአዴግ መሬት የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ንብረት ነው፡፡›› በሚል ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ተዘዋውረው የመስራትና የመኖር መብታቸውን ስለገደበና በዚህ የተሳሳተ ፖሊሲ ኢትዮጵያ እንደ አገር ትልቅ ችግር እየገጠማት በመሆኑ ችግሩ ከሚደርስባቸው ዜጎች ጎን በመሆንና ሌላውን ህዝብ በማንቀሳቀስ ኢህአዴግ ሃገር የማስተዳደር አቅምም ሆነ ችሎታ እንደሌለው በማጋለጥ ስልጣኑን እንዲለቅ ግፊት ለማድረግ እንደሆነ አቶ ብርሃኑ ለነገረ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል፡፡ የክሱን ሂደትም ሚዲያውያና ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲከታተሉት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Source: Negere Ethiopia

NE8
Previous Story

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 8 – ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮችን ይዛ ቀርባለች

Next Story

ጓዶች በአፅቢ ከተማ አራት የዓረና አመራር አባላት ከያዙት አልጋ እንዲለቁ ተጠይቀው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ታስረው አደሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop