Hiber Radio: ለጋምቤላው እልቂት ሳሞራ የኑስ እና ጄ/ል አብርሃ ማንጁስ ተጠያቂዎች መሆናቸው ተገለጸ – (ልዩ ዘገባ በጋምቤላና በወቅታዊው የሃገራችን ጉዳይ)

/

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
የህብር ሬዲዮ ሚያዚያ 10 ቀን  2008 ፕሮግራም

… በጋምቤላ የተከሰተው ግድያ ድንገተኛ አደጋ አይደለም በተደጋጋሚ እየተሰነዘረ የነበረ ጥቃት ነው።  ራሳቸው የሕወሓት ባለስልጣናትየሚያውቁት ነው። ጠረፍ ጠባቂ ማድረግ ሰራዊት እዛ መኖር ነበረበት ሀላፊነቱ የመንግስት ነው…መፍትሔው ይሄን ስርዓት መለወጥ ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ላይ ጫና መፍጠር ሕዝቡ በአንድ ላይ ለመብቱ እንዲቆም ማድረግ ካልተቻለ ግድያው ትላንትም ነበር ዛሬ አለ ነገም…>አቶ ኦባንግ ሜቶ የትብብር ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች  የተወሰደውን ግድያ አስመልክቶ  ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ     (ሙሉውን ያዳምጡት)

…ሰራዊቱ የሕወሃት ባለስልጣናትን ንብረት፣የነሱን ስልጣን ጠባቂ አድርገውታል። ኦሮሚያ ላይ ከፍተኛ ሰራዊት አላቸው፣በመሐል አገርበተለይም ከፍተኛ ቁጥር ያለው በሰሜን እዝ አለ ። ባለፈው በኤርትራ ወጣቶች ተወሰዱ ሲባል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰራዊት አንቀሳቅሰዋልዛሬ ግን ሰው እንኳን ሞቶፈጣን እርምጃ አልወሰዱም በዚህ ጥፋት ተጠያቂዎቹ የሰራዊቱ አመራሮች ናቸው።ሰራዊቱ ግን በአሁኑ ወቅትእየጠየቀ ነው …> ኮሎኔል ደረሰ ተክሌ የቀድሞ የሰራዊቱ የጥናትና ፕላን ክፍል ሀላፊ በጋምቤላ የተከሰተውን ግድያ አስመልክቶ ለህብርከሰጡት ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡት)

…በጋምቤላ የተወሰደው ግድያ ከደቡብ ሱዳን ድንበር ጥሰው የገቡት የሙርሌ ታጣቂዎች ግድያ ሲፈጽሙ የዛሬው የመጀመሪያ አይደለም።ከሳምንት በፊት ፉኢዶ ላይ ሃያ አኙዋኮችን ገለው ከብት ዘርፈው አፍነው የወሰዱዋቸውን ሶስት ህጻናት ገለዋል። የወያኔ ባለስልጣናት ያሉትየለም። ሕዝቡን ትጥቅ አስፈትተው እርስ በእርሱ ከፋፍለው እየገደሉና እያስገደሉ ያሉት እነሱ ናቸው…ስርዓቱ ካልወደቀ ግድያውአይቆምም።…> አቶ ኡዶል ኡጁሉ የታህሳስ ሶስት መታሰቢያ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ዋና ጸሐፊ የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በጋምቤላ በንጹሃንላይ የፈጸሙትን ግድያ አስመልክቶ ከሰጡን ቃለ ምልልስ(ቀሪውን ያዳምጡ)

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአብይ አህመድ የአማራን ህዝብ ንቀት! በእሳት እየተጫወቱ መሆኑን ሊያውቁት ይገባል -ሕብር ራዲዮ

በሊቢያ በረሃዎች እና የባሕር ዳርቻዎች ላይ የዛሬ ዓመት በአረመኔዎቹ አይሲስ ታጣቂዎች በግፍ ስለተገደሉት 30 የሚጠጉ ወገኖቻችን ቅዱስመጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? ቁርዓኑስ? ስለ ከፈሉት ሐይማኖታዊና ኢትዮጵያዊ ተጋድሎ የሚዘክር መሰናዶ(ልዩ ጥንቅር)

በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ሕዝባዊ ንቅናቄ በአገዛዙ የመብት ረገጣ እየተዳከመ ነው? የተቃውሞ አመራሮች ተገቢውን አመራር ሰጥተዋል እናሌሎችን ወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክቶ ከቢቢኤኑ ዋና ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ሳዲቅ አሕመድና ከአንሃፋው ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ ጋርያደረግነው ሰፋ ያለ ውይይት የመጀመሪያ ክፍል(ያዳምጡት)

ኦቲዝም እና ልጆቻችን ወላጅና ባለሙያ ምን ይላሉ ቃለ መጠይቅ ተካቷል(ያዳምጡት)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

በጋምቤላ በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች ለተገደሉት ከ200 በላይ ንጹሃንና ለታፈኑት  ከመቶ በላይ ህጻናት የምዕራብ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል አብረሃማንጁስና ኤታማዦር ሹሙ ሳሞራ የኑሱ ተጠያቂዎች መሆናቸው ተገለጸ

ከግድያው የተረፉ እማኞች የክልሉን የዘገየ እርምጃ አውግዘዋል

አባዱላ ገመዳ ኢህአዴግ መቶ በመቶ በተቆጣጠረው ፓርላማ ተቀምጠው ጸሎት እንዲደረግላቸው መጋበዛቸው የስርዓቱ ደጋፊዎችን ጭምርአስቆጣ

የጋምቤላውን ጥቃት ተከትሎ ኢትዮጵያውያን የአገሪቱን ድንበር መጠበቅ የተሳነው አገዛዝ ላይ ቅሬታቸውን ማቅረብ ቀጥለዋል

የአረብ ኢሚሬት በአሰብ ወደብ ላይ ወታደራዊ ተቋም መገንባት ለኢትዮጵያ ስጋት መሆኑ ተነገረ

ኮስታሪካ በህገወጥ መንገድ ወደ ግዛቴ ገቡ ያለቻቸውን ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ዳግም ወደ ፓናማ ማባረሯ በሁለቱ አገሮች መካከልውጥረት ፈጠረ

በጣሊያኑ ላምባዱሳ ደሴት አቅራቢያ ለሰጠሙት ወገኖቻችን ተጠያቂ የሆነው ግለሰብ ጣሊያን ውስጥ ቅጣቱን አገኘ

ለስልጣኑ የሰጋው የኢትዮጵያው አገዛዝ የፈለገውን ኮምፒዩተር ለመሰለልም ሆነ የዜጎችን የዲጂታል እንቅስቃሴ ለመገደብ ሕግ አርቅቆ አቀረበ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

Share