ሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 135 ሰዎችን በሽብርተኝነት ክስ አሰረች

(ዘ-ሐበሻ) ሳዑዲ አረቢያ 135 ሰዎችን በሽብርተኝነት ጠርጥራ ማሰሯን አስታወቀች:: የሳዑዲ መንግስት እንዳስታወቀው በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ከታሰሩት 135 ሰዎች ውስጥ 109ኙ የራሷ ዜጎች ሲሆኑ ቀሪዎቹ 26 ሰዎች ከኢትዮጵያ; ከሶሪያ; ከየመን; ከግብጽ; ከሊባኖስ; ከአፍጋኒስታን; ከባህሬን እና ከኢራቅ ዜግነት ካላቸው መሆኑን ዘ-ሐበሻ ከሳዑዲ ሚዲያዎች ካገኘችው መረጃ መረዳት ተችሏል::

ከአክራሪዎች; ከአሸባሪ ቡድኖች; ከታገዱ የሽብር ኃይሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር, የነርሱን ዓላማ በማሰራጨት, ድብድብ በማንሳትና በሌሎችም ወንጀሎች የተከሰሱት ወገኖች ምን ዓይነት ፍርድ እንደሚጠብቃቸው ሚድያዎቹ የገመቱት ነገር የለም::

በከተማ ውስጥ በሽብር ከተፈረጁ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት በፍጠር የተለያዩ የማቃጠል, የማፈንዳት, ሰዎችን በመግደል አንዳንድ ሽብር ወንጀሎች የተጠቀሰባቸው እነዚሁ ወገኖች ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እንደሚታይ ይጠበቃል::

የሳዑዲ ሚዲያዎች ከታሰሩት ውጥ ኢትዮጵያውያን ዜጎች እንዳሉበት ይግለጹ እንጂ ስለቁጥራቸው ብዛት ያሉት ነገር የለም::

ተጨማሪ ያንብቡ:  በእነሀብታሙ አያሌው ጉዳይ ማረሚያ ቤት ላይ ክስ ቀረበ

2 Comments

  1. አንድ ኢትዮጵያዊ ብቻ ነው የተባለው። እሱም በትክክል ኢትዮጵያዊነቱ እስኪረጋገጥ እንደ ዜና ይዘነው የሚቆይ ይሆናል።

Comments are closed.

Share