በጅማ ዩኒቨርሲቲ ጉዳይ የተከሰሰው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ዋስትና ተከለከለ፤ “የኦሮሞ ህዝብ ታላቅ እንደሆነ አምናለሁ”

“የተከሰስኩበት ጽሁፍ የሌላ ሰው በመሆኑና ኤዲቶሪያል ላይ የወጣ ባለመሆኑ የመጽሔቱ አቋም ተደርጎ መወሰድ የለበትም፡፡” ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ከዳዊት ሰለሞን

በእንቁ መጽሔት የመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ዕትም አምሳሉ ገ/ኪዳን የተባሉ ጸሐፊ ለንባብ ባበቁት ጽሁፍ መነሻነት በጅማ ዩኒቨርስቲ ሁከት ተቀስቅሶ ንበረት ሲወድም በተማሪዎች ላይ የአካል ጉዳት በመድረሱ ዩኒቨርስቲው በዋና አዘጋጁ ኤልያስ ገብሩ ላይ ክስ አቅርቧል በማለት አራዳ ለሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያስረዱት ረዳት ሳጅን ፍሬህይወት ሰርጸ ተጠርጣሪው ዋስትና ተከልክሎ መረጃ እስክንሰበስብ የአስራ አራት ቀን ይፈቀድልን ብለው ነበር፡፡

የመጽሔቱ ዋና አዘጋጅ ኤልያስ ገብሩ በበኩሉ ህገ መንግስቱ ላይ የተፈቀደውን ሀሳብን የመግለጽ መብት በመንተራስ የወጣው የፕሬስ ህግ ጋዜጠኞች ዋስትና ማግኘት እንደሚገባቸው በመደንገጉ ጉዳዩን በውጪ ሆኜ እንድከታተል ፍርድ ቤቱን እጠይቃለሁ፡፡የተከሰስኩበት ጽሁፍ የሌላ ሰው በመሆኑና ኤዲቶሪያል ላይ የወጣ ባለመሆኑ የመጽሔቱ አቋም ተደርጎ መወሰድ የለበትም፡፡እኔ በግሌ የዚህ ጽሁፍ ተቃዋሚ ነኝ ይህንን ጽሁፍ የሚቃወም ሌላጽሁፍ አትመን አሰራጭተናል፡፡በግሌ የኦሮሞ ህዝብ ታላቅ ህዝብ እንደሆነም አምናለሁ››ብሏል፡፡

ዋስትና የሚያስከለክል ክስ ባይቀርብበትም ‹‹ፖሊስ ከጉዳዮ ጋር በተያያዘ የሚያጣራው ነገር በመኖሩ የሰባት ቀን ጊዜ ፈቅጃለሁ››ያሉት ደግሞ ዳኛው ናቸው፡፡በዚሁ መሰረትም ኤልያስ ግንቦት 26/09/2006 ፍርድ ቤት ይቀርባል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ቃሊቲ ተዛወረ

3 Comments

  1. @freedom-
    ante beqa yehonk luti barya hone demo ye keye damaun ewnetenjawin ethiopiawi yemeni new tilalek? minew ante ye parlama temerachu girma seyfu nehe ende? turura barya eko ethiopiawi ayedelem-ke mengistu hailemaryam jemiro-
    yemegermew neger liju melkum ene memselu new

  2. >>>ኢህአዴግ የገጠመውን የኪራይ ሰብሳቢ፣የሙሰኛ፣ጥቅማጥቅመኖች የእኔ የእኔ ብቻ አትድረስብኝ ያንተን እንካፈል… ቁርሾ አመፅን ቀስቅሶ ንብረት ሲያወድም፣ ባንክ ሲያዘርፍ፣ ግለሰቦች የለፉበት ንብረት በእሳት ሲቃጠል…ሞኝ ያገኘው ፈሊጥ! “የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተደበደቡ፣ አበዱ፣ ፈነዱ፣ አለቁ” እያሉ ቁስለኛና እሬሳ በመቁጠር የግል የፓለቲካ ፍጆታቸውን በድሃ ልጅ ደም ሲያባዙ ሲያካፍሉ የከረሙት የኢህአዴግ ደጋፊና-ተደጋፊ.. ተቃዋሚና- ተቋቋሚ አንዲሁም መሐል ሰፋሪው እነ ጭር ሲል አንወድም አጋር ፓርቲዎችን ጨምሮ ከቀበሌ-እስከ ክልል ከገጠር እስከ አህጉር ሲቀውጡት ሰነበቱ።

    **ህወአት/ኢህአዴግ ምኑ ሞኝ ነው የተካናበትን ዘዴ…ለተጎጂው ኦሮሞ ጭዳ ማቅረብ ስላለበት “አቶ ኤሊያስ ገብሩን ወደ መሰዊያው አቀረበ” የኦሮሞ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ሕገ-መንግስቱን ጥሶ ሳያስፈቅድ ንብረትና ሰው እያጠፋ ሰላማዊ ሰልፍ እያለ ሲቀውጠው አልተጠየቀም ጭራሽም ሕገ-መንግስታዊና ተገቢ ጥያቄ ተባለ።(ለመሆኑ በጋራ ማስተዳዳርና የከተማ ልማት የሚከለክል ህገመንግስት አለ? ለመሆኑ ሕዝቤ መንገድ ጤና ጣቢያ መጓጓዣ የጥቃቅን አንዱስትሪ ባላቤትና ተጠቃሚ አይሁን ‘ገበሬና ሁለት በሬ’ ብቻ የሚል ዜጋ የየት ሀገር ሰው ነው? ለመሆኑ ይህ ሁሉ ወጣት ተምሮ ት ሊሄድ ነው? ምን ሰርቶ ቤተሰብ ሊመሰርት ነው!?ድሃው ገበሬ አይለፍለት ቋንቋውና ዘለዓላም የኖረበት የኩበት ጭስ..የአልቅት ውሃ..የድንጋይ መደብ ለወገቡ ፈረደበት ማነው? በእርግጥ የእነኝህ የመካካለኛና ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ሥርዓት ብቃትና ጥራቱ አይንና ጆሮ አዕምሮ ባለው ሰው ይመራል? ወይንስ ያው ልማታዊ ካድሬ መፈልፈያ ሆኗል የሚባለው እውነት ነው።? እኛ ከውስጥ እናንተ ከውጭ ድረሱ ተብሎ በቅንጅት የተሰራውን አመፅና ሽብር ያልታወቁ ግለሰቦች ተቀላቀሉበት ይላሉ።ያልታወቀ ግለሰብ እንዴት በከተማውና በሀገሩ ኖረ? መሳሪያ ከየት አመጣ? ምን አልባት የክልሉ ፖሊስ ደህንነት አቀብሎ ይሆን? ቀድሞም “ክርስቲያን ቀና ብሎ ካየን አንገቱን በሜንጫ እንለዋለን ሲሉ ከፓለቲካ ተንታኝነት ወደ ፖለቲካ በታኝነት የመከላከያውንና ፖለቲካል ኢኮኖሚውን በአመፅ እንነጥቃለን የሚሉትን በኢህአዴግ በውስጥ ክንፍ አድርጎ በጂነዲን ሳዶ ሚስጥር አቀባይነት ለተቀነባባረው ሴራ ወይንም ከኢህአዴግ በሥነምግባር ጉድለት ተባረው ዛሬ ዙሪያውን በማዋቀጥ ተልካሻ የታሪክ መፅሐፍ በመቸርቸር ግን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሆነው ወጣቱን ለፀብ የሚጋብዙትን ሰላም በማደፍረስ የልማት የሀገር ሰላምና ዕድገትን የሚያደናቅፉትን መንግስት እየረዳና እየተንከባከበ ያላቸውን ሕጋዊ የፓርቲ ፍቃድ የሚያስነጥቅ አመፅ በግላጭ በአደባባይ መፈክር እያሰሙ ሲቀሰቅሱ ምንም በቂ እርምጃ ሳይወስድ በንጹሃን ደካማ ጋዜጠኞች(ተቺ) ፀሀፊያን ላይ የሚደርሰው አፈናና እንግልት፣ አድሎዓዊ እስር ..ከሜንጫ እስኪሪብቶ ጋዜጣና ትችት ከፈራ በእውነቱ ኢህአዴግ ከነበረበት ደረጃ በጣም ዝቅ ያደረገው ድሃ ታጋዮች የተሰውለት ዓለማና ተግባሩ ሁሉ በጥቂት ጥቅማጥቅመኞችና አስመሳይ አድርባዮች የተጠለፈበት አንደሆነ ሊረዳ ይገባል። “መድረክ ሲፋቅ ኢህአዴግ” ነው ማለቱ ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል!!!ይታሰብበት>>>ሐሳብን በሀሳብ መሞገት እነጂ አትፃፍ አታፅፍ ማለት አድሎዓዊ በቀል የፈሪ ዱላ ያስመስላል በግለሰቡ ጋዜጣ ላይ ተፃፈ ለተባለው ነጥብ ሞጋች ፅሑፍ ማውጣት ብልህነት ነው።አራት ነጥብ። “ንብረትና የሰው ህይወት ያጠፋነው የተፃፈ አንብበን ጭንቅላታችን ተናውጦ ነው” የሚለው የየዋህ መከላከያ መልስ ግን “ነጻ እንድናወጣችሁ አከሌን ክሰሱና ዴሞክራሲያዊነታችንን በበቀል እናሳያችሁ ተብለው ነው። ይህም ቢኒያም ከበደ በአምቦ ዩኒቨርስቲ ያነጋገራቸው ልጆች ቃል በቃል የተነገራቸው አስኪጠፋባቸው ግን በትክክል ዛሬ ግለሰቡ የተከሰሰበትን ነጥብ አስረድተዋል የኦሮሞ ጎምቱ ሊሂቃንም ያንኑ በተለያየ ሚዲያ አብራርተውታል ። ለምን ይዋሻል!? ሕዝብ እና መንግስት ህግ ማክበር አለበት…በዚህ ዘመን ውይይት እንጂ ንበረትም ሰውም መጥፋት የለበትም። የተማረ ያስተማር!ያልተማረ ይማር!ዕድገትና ብልጽግና በጋራ ለጋራ ለእኛ እነጂ ለእኔ ብቻ ማለት ይቅር።ሰላማዊ ጋዜጠኞች ፖለቲከኞች ጸሐፊያን ነፃ ይሁኑ በለው!

Comments are closed.

Share